Tag Archives: Article19

ዞን 9 ብሎገሮች ሌላ ቀጠሮ ተጠየቀባቸው፤ የፖሊስየ28 ተጨማሪ ቀናት ጥያቄ ውድቅ ተደርጓል

የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጠረጠርኳቸው ያላቸውን 9 ጋዜጠኞች እና ብሎገሮች ሚያዝያ 2006 ዓ.ም.ቢያስርም እስካሁን ምንም ዓይነት ህጋዊ ክስ ሳይመሰርት፤ ዛሬ ሰኔ 22 ቀን 2006ዓ.ም. በድጋሚ ተለዋጭ ቀነ ቀጠሮ ጠይቋል፡፡ ፖሊስ ለፌደራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ ወንጀል ችሎት ዛሬ ቀጠሮ የነበራቸውን እና በማዕከላዊ ያሰራቸውን የዞን 9 ብሎገሮች መካከል በፍቃዱ ኃይሉ፣ ማህሌት ፋንታሁን እና አቤል ዋበላን ይዞ ቢቀርብም፤ እንደተለመደው የቴክኒክ ምርመራዬን አልጨረስኩም፣ ከተሰከሳሾች የተገኙ መረጃዎች ተተርጉመው አላለቁም፣…የሚሉ ምክንያቶችን በመጥቀስ ተጨማሪ የ28 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ እንዲሰጠው መጠየቁ ተሰምቷል፡፡

hgtፍርድ ቤቱ እስካሁን የተሰጠው ጊዜ በቂ ነው በማለት የተጠየቀውን የ28 ቀናት ውድቅ ቢያደርግም፤ ፖሊስ ምርመራው አጠናቆ እንዲቀርብ የ14 ቀናት ጊዜ በመስጠት ለሐምሌ 6 ቀን 2006ዓ.ም.ተለዋጭ ቀነ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ይሁን እንጂ ዕለቱ እሁድ ቀን የሚውል በመሆኑ እና መዝገቡ ከእንግዲህ በተዘዋዋሪ ተረኛ ዳኛ ሳይሆን በመደበኛ ችሎት መታየት ስላለበት ለሰኞ ሐምሌ 7 ቀን 2006 ዓ.ም. ከቀኑ 8፡00ሰዓት ተለዋጭ ቀነ ቀጠሮ መሰጠቱን ከተከላካይ ጠበቃቸው አቶ አምሃ መኮንን መረዳት ተችሏል፡፡ ጉዳዩ ሲታይ የነበረው ከሌሎች ቀናት በተለየ ዛሬ ቤተሰብም በችሎቱ ላይ እንዳይታደም ተከልክሏል፡፡

በፍርድ ቤቱ ግቢ በርካታ የእስረኞቹ ቤተሰቦች፣ ወዳጅ ዘመዶች፣ ዓለም አቀፍ ዲፕሎማቶች እና ጋዜጠኞች ቢገኙም አንዳቸውም ችሎቱን እንዲከታተሉ አልተፈቀደም ነበር፡፡ ፖሊስ ያሰራቸውን ተጠርጣሪዎች ይዞ ወደ ችሎት ሲገባ በፍርድ ቤቱ ግቢ ችሎቱን ለመታደም ከመጡት መካከል ዮናታን ተስፋዬ እና ምኞት የሚባሉ ወጣቶችን በሞባይል ፎቶ ለማንሳት ሞክራችኋል በሚል ወደ ማዕከላዊ ይዟቸው የሄዱ ሲሆን፤ ከሰዓታት በኋላ መለቀቃቸው ታውቋል፡፡ በተመሳሳይ መልኩ እስካሁን ምንም ክስ ሳይመሰረትባቸው በእስር ላይ የሚገኙት ቀሪዎቹ 6ቱ ጋዜጠኞች እና ብሎገሮች የፊታችን ሐምሌ 5 ቀን 2006 ዓ.ም. ጠዋት ቀነ ቀጠሮ እንዳላቸው ይታወቃል፡፡

ፍርድ ቤቱ ባለፈው ውድቅ ያደረገውን ጉዳይ ዛሬ ያለምንም ይግባኝ ማፅደቁ ተሰማ

ዛሬ ግንቦት 24 ቀን 2006 ዓ.ም. የነበረው የፍርድ ቤት ውሎ አዲስ ክስተትን ይዞ ብቅ ማለቱ ተሰምቷል፡፡ ባለፈው ሚያዚያ 2006 ዓ.ም.ተጠርጥረው ከታሰሩ 3 ጋዜጠኞች እና 6 ብሎገሮች መካከል ዛሬ እሁድ ግንቦት 24 ቀን 2006 ዓ.ም. ቀጠሮ የነበራቸው በፍቃዱ ኃይሉ፣ አቤል ዋበላ እና ማህሌት ፋንታሁን ቀደም ሲል የማዕከላዊ ፖሊስ ጉዳዩን ወደ ፀረ-ሽብርተኝነት የክስ ጉዳይ ለመውሰድ የጠየቀው በፍርድ ቤቱ ውድቅ ተደርጎ የነበረ ቢሆንም፤ ዛሬ በሌላ ተቀያሪ ወንድ ዳኛ እዛው ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ ወንጀል ችሎት ባለፈው በነበረው ቀጠሮ ውድቅ የተደረገው በፀረ-ሽብርተኝነት ክስ ፖሊስ የጠየቀው ተጨማሪ 28 ቀናት የምርመራ ጊዜ ተቀባይነት አግኝቷል፡፡ በዚህም መሰረት ፍርድ ቤቱ በዛሬው ውሎ የነበፍቃዱ ፣ አቤል እና ማህሌት ሂደት ለሰኔ 22 ቀን 2006 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀነ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
FF
በጉዳዩ ላይ ጥያቄ ያቀረብንላቸው ተከላካይ ጠበቃ አቶ አምሃ መኮንን፤ ከህግ አኳያ ፖሊስ ጉዳዩን ወደ ፀረ-ሽብርተኝነት ጠይቆ ውድቅ ተደርጎበታል፣ ስለዚህ በነበረው ውሳኔ ፖሊስ ቅር ከተሰኘ ይግባኝ ማለት እንጂ በተመሳሳይ ችሎት እና ጉዳይ ላይ በፍርድ ቤቱ ውድቅ የተደረገ ጉዳይ እንደገና ቀርቦ የፖሊስ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱ እና ተጨማሪ የ28 ቀናት የምርመራ ጊዜ በሚል መፈቀዱ ከህግ አግባብ ውጭ ነው፤ ይሄንንም ለፍርድ ቤቱ ብናቀርብም ተቀባይነት አላገኘም፤ ስለዚህ የህግ አካሄድ (procedure) ስህተት ታይቶበታል ሲሉ የነበረውን ሂደት ተናግረዋል፡፡ ይህን የክስ ሂደት ፖሊስ ጉዳዩን ወደ ፀረ-ሽብርተኝነት ለመውሰድ ውድቅ ያደረገችው ዳኛ ሴት እንደነበረች አይዘነጋም፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ፤ የነገረ-ኢትዮጵያ ጋዜጠኛ በላይ ማናየ ፖሊስ ፍርድ ቤት ያቀረባቸውን እስረኞች ሲያወጣ፤ ለተወሰነ ጊዜ በጠበቂ የፀጥታ ኃይሎች ለጊዜው ታግቶ እንዲቆይ ከተደረገ በኋላ፤ ለነገ ማዕከላዊ እንዲቀርብ ትዕዛዝ በመስጠት ተለቋል፡፡ ለተወሰነ ጊዜ የተደረገው የጋዜጠኛው እገታ ምክንያት እስካሁን አልታወቀም፡፡

ጋዜጠኞች እና ብሎገሮች ቶርቸር እንደተፈፀመባቸው ተገለፀ

 

ዛሬ ሚያዚያ 30 ቀን 2006 ዓ.ም. ፍርድ ቤት የቀረቡት በፍቃዱ ኃይሉ፣ አቤል ዋበላ እና ማህሌት ፋንታሁን ከሰዓት በዋለው የአራዳ ምድብ 1ኛ ወንጀል ችሎት ቀርበዋል፡፡ በፍቃዱ ኃይሉ የውስጥ እግሮ ተደብድቦ ቶርቸር መደረጉን እና አቤል ዋበላም ከፍተኛ ተደጋጋሚ ድብደባ እንደተፈፀመበት ለፍርድ ቤቱ ተከተፈቀደላቸው ቤተሰቦች እና ከተከላካይ ጠበቃቸው አቶ አምሃ መረዳት ተችሏል፡፡ በስፍራው ልክ እንደ ትናንቱ በርካታ ጋዜጠኖች፣ ቤተሰቦች፣ ወዳጆች እና ዓለም አቀፍ ዲፕሎማቶች ተገኝተው ነበር፡፡ ነገር ግን ከጥቂት ቤተሰብ በስተቀር ጋዜጠናም ሆነ ዲፕሎማት እንዲሁም ጓደኞቻቸው ችሎቱን እንዲታዘቡ አልተፈቀደም ነበር፡፡ናግረዋል፡፡ ማህሌት ፋንታሁን በችሎት ላይ ከማልቀስ በቀር ቃላት መናገር እንዳልቻለች በችሎቱ
ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ የተፈፀመውን ቶርቸር ለማስተባበል መሞከሩን እና እነ በፍቃዱ ኃይሉና አቤል ዋበላን ውሸታቸውን ነው፣ እነኚህ የድርጊቱ ዋና አቀናባሪ ናቸው ሲል መናገሩን ከችሎት ታዳሚ ቤተሰብ መረዳት ተችሏል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ፖሊስ የያዘበትን ምክንያት ሲያስረዳ ከአሸባሪ ድርጅቶች ጋር በመተባበር ከምርጫው በፊት አመፅና ሽብር ለመፈፀም 5 ጊዜ ውጭ ሀገር ስልጠና ወስደዋል፣የመገናኛ ብዙኃን መሳሪያ ኮምፒዩተር ገዝተዋል ማለቱን ጠበቃቸው አቶ አምሃ ለመገናኛ ብዙኃን ገልፀዋል፡፡ ይሁን እንጂ ፖሊስ አሸባሪ ያላቸውን እና ስልጠና የሰጡትን ድርጅቶች ስም እንዲጠቅስ ሲጠየቅ አልጠቅስም፣ አሁን ከጠቀስኩኝ ተባባሪዎቻቸው ያመልጡኛል ሲል ለፍርድ ቤቱ መናገሩን መረዳት ተችሏል፡፡zz
ከዛሬ ጀምሮም የቅርብ ጥቂት ቤተሰብ ብቻ ማዕከላዊ ሄዶ እንዲጎበኛቸው የተፈቀደ መሆኑን በመግለፅ ለእሁድ ግንቦት 10 ቀን 2006 ዓ.ም. ጠዋት ተለዋጭ ቀነ ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡ የትናንትናው የነ ተስፋዓለም ወልደየስ፣አስማማው ኃይለጊዮርጊስ፣ ኤዶም ካሳዬ፣ ዘለዓለም ክብረት፣ ናትናኤል ፈለቀ እና አጥናፍ ብርሃን ችሎት ለቅዳሜ ግንቦት 9 ቀን 2006 ዓ.ም. ጠዋት መቀጠሩ ይታወሳል፡፡