Tag Archives: Ethiopia

ከ3 ወር በፊት የታፈነው የመኢአድ አመራር የት እንደደረሰ አልታወቀም

aeupየሶስቱ ፓርቲዎች አመራሮች ለታህሳስ 21 ቀን 2007 ዓ.ም ተቀጥሮባቸዋል
የገዥው ፓርቲ የደህንነት ኃይሎች የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችን ከየ ክፍለ ሀገሩ ማሰር በጀመሩበት ወቅት በደህንነትና ፖሊሶች የታፈነው የመኢአድ አመራር የት እንደደረሰ እንደማይታወቅ ቤተሰቦቹ መግለፃቸውን የነገር ኢትዮጵያ ዘገባ አመልክቷል፡፡ የሰሜን ጎንደር አመራር የሆነው አቶ ችሎት ባዜ መስከረም 2 ቀን 2007 ዓ.ም በገዥው ፓርቲ የደህንነት ኃይሎች የታፈነ ሲሆን፤ በወቅቱ ቤተሰቦቹ ወደ ማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ እንደተዛወረ መረጃ ደርሷቸው እንደነበር መግለፃቸው ተጠቁሟል፡፡ ሆኖም በተደጋጋሚ አቶ ችሎት ወደ ማዕከላዊ መዛወር አለመዛወሩን ቢጠይቁም እንዳልመጣ ተነግሯቸዋል፡፡

የታፈነው የመኢአድ አመራር ማዕከላዊ እንደሌለ የተነገራቸው ቤተሰቦቹ ፍርድ ቤት ቀርቦ ከሆነ በሚል ሪጂስትራል ስሙ እንዳለ ቢያስጠይቁም እስካሁን ፍርድ ቤት እንዳልቀረበ አረጋግጠናል ብለዋል፡፡
በሌላ በኩል ከየ ክፍለ ሀገሩ በገዥው ፓርቲ የደህንነት ኃይሎች ታፍነው በአሁኑ ወቅት ማዕከላዊ የሚገኙት የሰማያዊ፣ የአንድነት እና የመኢአድ አመራሮች በትናንትናው ዕለት አራድ ምድብ ችሎት ቀርበው ለታህሳስ 21 ቀን 2007 ዓ.ም ተቀጥሮባቸዋል፡፡

Nine Ethiopian Journalists and bloggers were arrested

The journalists and bloggers were arrested by Ethiopian government on April 25-26, 2014. The journalists Asmamaw Hailegiorgis,  Tesfalem Woldeyes and Edom Kssaye from Addis Guday and Addis Standard magazine  respectively arrested. As the same time, 7 Ethiopian zone 9 bloggers and activists were also arrested.

zonThe bloggers and activists Befekadu Hailu, Atnaf Birhan, Mahlet Fantahun, Natnael Feleke, Abel Wabela and Zelalem Kibret   arrested at Maikelawi criminal investigation bureau of Addis Ababa police but still no charge at court related with them.

 

 

በኦሮሚያ ሻኪሶ ሁለት ተማሪዎች በፌደራል ፖሊስ በመገደላቸው ውጥረት መንገሱ ተሰማ

 

በደቡብ ኢትዮጵያ ኦሮሚያ ክልል በሚገኘው ጉጂዞን ኦዶ ሻኪሶ ከተማ በተማሪዎችና በከተማው አስተዳደር መካከል በተፈጠረ አለመግባባት የፌደራል ፖሊስ ጣልቃ በመግባት በወሰደው የኃይል እርምጃ አንዲት ሴት እና አንድ ወንድ በአጠቃላይ ሁለት ተማሪዎች ህይወት በማለፉ እና ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ በመቁሰላቸው የኦዶ ሻኪሶ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ተቃውሟቸውን ማሰማታቸው ተጠቁሟል፡፡ pic

የግጭቱ መንስኤ ተማሪዎቹ “በከተማውና አካባቢው የመጠጥ ውሃ አገልግሎት የለም፣ አንድ ባለ 25 ሊትር ጀርካን ውሃ በ 7 ብር እየተሸጠ ነው፣ በቂ የመብራት አገልግሎትም የለም፣ ከህዝቡ ሚሰበሰበው ግብር እና ከመንግስት የሚመደበው በጀት እስካሁን ምን ላይ እየዋለ ነው? ህብረተሰቡም እኛ ምበውሃጥም እየተጎዳን አስተዳደሩ እስከዛሬ ለምን ዝም አለ?” የሚሉ ጥያቄዎች በመነሳታቸው፤ የአስተዳደር አካላት ተማሪዎቹን “እናንተ ምን አገባችሁ፣ አርፋችሁ ተማሩ፤ካልሆነ እርምጃ እንወስዳለን” የሚልምላሽ በመሰጠቱ ተማሪዎችን እንዳስቆጣ የደረሰን መረጃ አመልክቷል፡፡ በዚህም ምክንያት የፌደራል ፖሊስ ድንገት ጣልቃ በመግባት ተቃውሞ በሚያሰሙ ተማሪዎች ላይ እርምጃ በመውሰዱ የከተማው ነዋሪዎችም ተቃውሞውን መቀላቀላቸው የአዲስሚዲያ ምንጮች ከስፍራው ጠቁመዋል፡፡ በዚህም ምክንያት የከተማውና የአካባቢው ነዋሪ ከፌደራል ፖሊስ ጋር መፋጠጡን፣ ይህ እስከተዘገበበት ሰዓት ድረስም በከተማው የጦር መሳሪያ ተኩስ ሁሉ እየተሰማ መሆኑንም ምንጮች አረጋግጠዋል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ የሟቾቹ ሁለቱ ተማሪዎች አስከሬን በሆስፒታል እንደሚገኝ እና ወላጆችም ወደሆሲፒታሉ እንዳይገቡ በፌደራል ፖሊስ መከልከላቸው እንዲሁም በከተማው ተወስኖ የነበረው ቁጣም ወደ ገጠሩ ነዋሪበ መስፋፋት በርካቶች በቁጣወደ ከተማው እየገቡ መሆኑንም ምንጮች አስረድተዋል፡፡ ይህንንም ተከትሎ በከተማው ከፍተኛው ጥረት መንገሱም ተጠቁሟል፡፡

እንደምንጮች ገለፃ ከሆነ ችግሩ የተፈጠረው የኦዶ ሻኪሶ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የመብት ጥያቄ በማንሳታቸው አስተዳደሩ ጥያቄያቸውን በቀጥታ ወደ ፖለቲካ በመቀየር የፌደራል ፖሊስ ተጠርቶ በቀጥታ የኃይል እርምጃ በመውሰዱ የሁለት ተማሪዎች ህይወት ወዲያው በማለፉ መሆኑም ተጠቁሟል፡፡ በአሁን ሰዓትም በከተማው በተለያዩ ቦታዎች የእሳት ቃጠሎ፣ የህንፃዎች መስታወት መሰባበር፣ ሌሎች ንብረቶች እየወደሙ መሆናቸውን እንዲሁም ከፍተኛ የተኩስ ድምፅ እየተሰማ መሆኑንም ምንጮች አስታውቀዋል፡፡ አዲስሚዲያ ይህንን ለማጣራት የኦሮሚያ ፖሊስ አዛዥ ናቸው ወደተባሉት ኮማንደር አበበ እና የጉጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ገዳ ሮቤ ጋር ተደጋጋሚ ጥረት ቢደረገም ለጊዜው አልተሳካም፡፡ ኦዶ ሻኪሶ በኢትዮጵያ ከፍተኛ የወርቅ ማዕድን ከሚመረትባቸው አካባቢዎች ዋነኛው መሆኑ ይታወቃል፡፡

A Journalist kidnapped, Threatened, and Beaten by Intelligence and Security Agents in Ethiopia

By Betre Yacob

The Ethiopian journalist Bisrat Woldemichael was kidnapped, threatened, humiliated, and beaten by the Ethiopian intelligence and security agents on 28 August, 2013. He has reported this incident today to journalists.

Bisrat reported that the dreadful incident took place at Gotera, a place in the capital Addis Ababa as he was walking home from work. He said he was victimized for exercising his right to free expression in conjunction with the related right to press freedom.bis

Bisrat Woldemichael works for a magazine, Ebony, as Editor in Chief, and writes political articles on different Ethiopian private press outlets. He also blogs at http://www.addismedia.wordpress.com and http://www.ethiopiahot.wordpress.com. The journalist is known for his outspoken articles focused on the poor governance and pervasive human right violation, which are turning the oldest East African nation, Ethiopia, into a hell.

Violence against journalists is a common practice in Ethiopia, a country generally regarded as one of the most dangerous places to be a journalist. According to Amnesty International, during the past three years only, over 100 prominent journalists were brutally prosecuted on fabricated charges, and too many others were also subjected to harassment, intimidation, and other violence.

“It was 3:30 AM in the evening, and I was returning home from my workplace. 4 people came to me and said: ‘we need to ask you some questions. Two of them were dressed in black and their faces were almost covered with their caps”, Bisrat said, while narrating his ordeal to journalists.

“I first didn’t understand what was going on. I realized that I was in danger just when one of them put a knife on my stomach”, he noted. “When I saw the knife, I asked them: ‘Who are you? What do you need? But none of them gave me an answer, instead they warned me just to keep walking forward,” he explained.

“I didn’t do anything but followed them, because I was surrounded, and the guy also clearly told me he would stab me with the knife if I tried to challenge them. In addition, one of them had a gun”, Bisrat said.

From there Bisrat was taken to a place far away from the main road. The place he was taken to was quite dark and out of public sight.

“As soon as we reached there they told me they were disappointed at my articles I had recently written, particularly at the one which dealt about the wealth of the late Prime Minister Meles Zenawi ”, Bisrat said.

“They said: ‘Who are you to count the wealth of Meles Zenawi? Who are you to write about his family’s wealth? You have passed the red line!’ ” he explained.

The journalist said that the kidnappers violently interrogated him at length, for almost one hour, and threatened him to stop writing.

“They said: ‘here we are giving you a last warning. If you write any more for any media (or if you keep blogging), the consequence will be worse for you. If you need your life, stop wiring. Remember! It is a last warning’ ”, Bisrat explained.

The journalist said that this was not the end of the drama but the beginning. “They also insulted and humiliated me, and finally began to beat me.

Right after the incident, Bisrat was able to go to a nearby police station, to report the case. But, according to him, having heard the case, the police officers simply gave him an appointment for the coming mooring and let him go. Bisrat said that it took him several days to get the case registered.

“They are Watching Me”

Bisrat Woldemichael Bisrat said since the day he experienced the violence he has been under surveillance. “Few days ago, I saw them following me behind”, he explained adding “I know they are watching me very closely.”

But, in the face of such grave threats, Bisrat, a journalist who is committed to freedom of speech, has continued doing his job with courage. He continues writing about the political crisis, poor governance, and human right violation worsening in Ethiopia.

“I don’t have a choice. I am a journalist. There is nothing to do except writing what I see, hear, and feel.” Bisrat explained. He again and again made clear that no threats and tortures would make him stop writing.Bisrat3

The paper Tigers

Article 19 of the Universal Declaration of Human Rights, guarantees the right to freedom of expression saying that: “Everyone has the right to freedom of opinion and expression; this right includes freedom to hold opinions without interference and to seek, receive and impart information and ideas through any media regardless of frontiers. Likewise, the International Covenant on Civil and Political Rights (ICCPR), which Ethiopia ratified in 1993, and the African Charter on Human and Peoples’ Rights guarantee the right in a very clear way. They even impose formal legal obligations on state parties to insure this fundamental right is protected.

But, sadly, even in the presence of all these legal documents, Enjoyment of press freedom and freedom of expression still continue to be a far cry for Ethiopian journalists and bloggers as they experience violence while doing their job. They are harassed, threatened, humiliated, and arbitrary jailed.

መብራት ለኤርትራ በነፃ ከተሰጠ ለእኛስ?

 

ብስራት ወ/ሚካኤል

ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይልን ለመጀመሪያ ጊዜ የተጠቀመችው በዘመነ ዳግማዊ አጼ ምኒሊክ አባ ሳሙኤል በሚባል ስፍራ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ፤ ጊዜው በ1890 ዓ.ም. ሲሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ከውሃ ኃይል ማመንጨት የተጀመረው ግን በ1904 ዓ.ም. ከአቃቂ ወንዝ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመረጃ ምንጮች ያስረዳሉ፡፡ በአሁን ሰዓት ግን አድጎ በርካታ ግድቦች በአጼ ኃይለስላሴ፣ በደርግና በኢህአዴግ ዘመን ተሰርተው ጥቅም ላይ ውለዋል፡፡

ከውሃ ኃይል የሚሰሩ የኤሌክትሪክ ግድቦች እየተሰሩ ቢሆንም የአቅርቦት እጥረትና የጥራት አገልግሎቱ ጥያቄ እያስነሳ ይገኛል፡፡ በተለይ አሁን አሁን መብራት ድንገት የመጥፋቱ ነገር ከምን የተነሳ እንደሆነ እስካሁን ባይገለፅም አዲስ አበባን ጨመሮ በተለያዩ የክልል ከተሞችም በተደጋጋሚ ይቋረጣል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘም ተጠቃሚዎች መብራት እንደሚጠፋ በኮርፖሬሽኑ ቀድሞውኑ የተነገራቸው ባለመሆኑ አገልግሎት እየሰጡ ያሉ የኤሌክትሮኒክስ መሳሪዎች ከጥቅም ውጭ እየሆነ ለወጭ የተዳረጉ ቢኖርም ከድርጅቱ የተሰጠም ሆነ የሚሰጥ ካሳ የለም፡፡ በዚህም የንግድ ተቋማት ሆቴሎች፣ የኤሌክትሮኒክስ ሱቆች፣…ወዘተ ይገኙበታል፡፡power1

አመራሮቹም ቢሆኑ አልፎ አልፎ ድንገት የመብራት መቋረጥ ችግር ከለኃይል አቅርቦት የተፈጠረ ሳይሆን በቴክኒካል ችግር መሆኑን ሲገልፁ ቢሰማም ችግሩ ግን አሁንም ድረስ እንዳለ አለ፡፡ ተቋሙ ምንም እንኳ ከሀገሪቱ አንጋፋ ተቋማት አንዱ ቢሆንም ከዚህ በፊት ሲፈጠሩ የነበሩ ችግሮችን ሙሉ ለሙሉ መቅረፍ አልቻለም፡፡ በዚህም ምክንያት በኢንቨስትመንቱ እንቅስቃሴ ላይ የራሱ አሉታዊ ተፅዕኖ እንደሚኖረው ቢጠበቅም በተደጋጋሚ ከሚሰጡ ተመሳሳይ የቴክኒክ ችግር ከሚል መልስ ውጭ የተጠቀሰ ችግር የለም፡፡

በነ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የቦርድ ሊቀመንበርነት፣ በነ አቶ ምህረት ደበበ ዋና ስራ አስፈፃሚነትና እና በነ ብርጋዴር ጄነራል ክንፈ ዳኘው የቦርድ አባልነት የሚመራው ይህ ተቋም በውስጡ 12,172 ሰራተኞችን እንደያዘ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ ካሉት ሰራተኞች መካከልም በቅርቡ ከአስራ አንድ ያላነሱ ከፍተኛ ኃላፊዎች በሙስና ተግባር ተጠርጥረው ጉዳያቸው በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 15ኛ ወንጀል ችሎት እየታየ ይገኛል፡፡ እንደ አቃቤ ህግ ክስ ከሆነ ተጠርጣሪዎቹ ከ 25 ሚሊዮን ዶላር (ከ 471 ሚሊዮን ብር) በላይ የህዝብና የመንግስትን ጥቅም ማሳጣታቸውን ያስረዳል፡፡ ይሁን እንጂ በርካታ የኃይል ማመንጫፕሮጀክቶች እየተመረቁ መሆኑ በተደጋጋሚ ቢገለፅም አሁን ለሀገሪቱ ጥቅም እየሰጠ ያለው አቅም ግን ከ2000 ሜጋ ዋት እንደማይበልጥ የተቋሙ የመረጃ ምንጮች ያስረዳሉ፡፡

ዋና መስሪያ ቤቱን አዲስ አበባ ፒያሳ ደጎል አደባባይ ፊትለፊት ያደረገው ይህ ተቋም እስከ ፊታችን 2009 ዓ.ም. ድረስ የሀገሪቱን የመብራት ኃይል ፍጆታ ወደ 10,000 ሜጋ ዋት ከፍ ለማድረግ ቢያቅድም አሁን በቀሩት አራት ዓመታት ውስጥ ግን ቀሪውን 8,000 ሜጋ ዋት ከየት አምጥቶ ጥቅም ላይ እንደሚያውለው እንቆቅልሽ ሆኗል፡፡ ምናልባት የአባይ ግድብ ፕሮጀክት ከፊታችን በቀሩ 4 ዓመታት ውስጥ ቢጠናቀቅ እንኳ የኃይል ፍጆታውን ሊያሳድገው የሚችለው ወደ 8,000 ሜጋ ዋት ሲሆን ግድቡም ወዲያው አገልግሎት ይሰጣል ተብሎ አይጠበቅም፣ የግድቡ ውሃ ሙላት በራሱ እረጅም ጊዜ የሚጠይቅ በመሆኑ፡፡

በሀገሪቱ ያለውን የኢቨስትመንት ሴክተር ከማስፋፋት አንፃር የመሰረተ ልማቶች በአግባቡ መሟላት ትልቅ አስተዋፅዖ እንዳለው ቢታወቅም የህዝቡ ፍላጎትም ከዕለት ወደ ዕለት እየጨመረ መምጣቱ ከአሁኑ ሌሎች የኃይል አቅርቦት አማራጮችም ካልተወሰዱ ነገ ከፍተኛ የኃይል አቅርቦት ችግር መግጠሙ የማይቀር ነው፡፡ ይሄ ደግሞ እንደ ከዚህ በፊቱ ከተለያዩ ኢንዱስትሪዎች የሰራተኛ ቅነሳ በር በመክፈት የስራ አጥ ቁጥርንም አሁን ካለው ከእጥፍ በላይ ሊያሳድግ እንደሚችል ይገመታል፡፡

የኢትዮጵያ መንግስትም ለውጭ ምንዛሪ ሲል የዜጎችን ፍላጎትና አቅርቦት በአግባቡ ሳያሟላ ለጎረቤት ሀገሮች በተለይም ለጅቢቲ 200 ሜጋ ዋት በይፋ መሸጡን መረጃዎች ሲጠቁሙ፣ ለሱዳን 200 ሜጋ ዋት ደግሞ ለመሸጥ የመስመር ዝርጋታው ተጠነቆ ሙከራ ላይ እንዳለ እየተነገረ ይገኛል፡፡ በቀጣይም መንግስት ለኬንያም 500 ሜጋ ዋት ለመሸጥ ስምምነት ላይ መድረሱ የተጠቆመ ሲሆን ይህ መቼ እና እንዴት እንደሚተገበር ወደፊት አብረን የምናየው ነው፡፡ ምክንያት የአሀገሪቱ የኃይል አቅርቦትና ፍላጎት አሁንም ሙሉ ለሙሉ ተሟልቷል ማለት አይቻልምና፡፡እንደ መንግስት ከሆነ ግን ወደፊትም ለሰሜን እና ምስራቅ አፍሪካ የመብራት ኃይልን በመሸጥ ከቡና ንግድ በተሻለ የውጭ ምንዛሪን ለማግኘት ማቀዱ አይዘነጋም፡፡ ምክንያቱም መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ከሆነ ኢትዮጵያ የነፋስና ከእንፋሎት ኃይል ውጭ ከውሃ ግድብ የሚገኝ ብቻ 45,000 ሜጋ ዋት  የመብራት  ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት ያሳያልና፡፡

ከሰሞኑን በተለይ ባለፈው ሐምሌ 20 ቀን 2005 ዓ.ም. በተለያዩ መረጃዎች እንደተገለፀው እና ይህንም የኤርትራው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኦስማን ሳህል በለንደን ለኤርትራ ማኀበረሰብ ገለፁት እንደተባለው ከሆነ የኢትዮጵያ መንግስት ለኤርትራ 250 ሜጋ ዋት የመብራት ኃይል በነፃ ለመስጠት በራሺያ፣ በኳታር እና በቱርክ በኩል ድርድር መጠየቁ ተጠቁሟል፡፡ ይሄ ደግሞ መንግስት የራሱን ዜጋ ፍላጎት ሳያሟላ ከደሃ ህዝብ አንጡራ ሃብት የሚገነቡ ግድቦችን ለኤርትራ ለምን በነፃ መስጠት እንደተፈለገ እስካሁን አልተገለፀም፡፡ይህ እውን የሚሆን ከሆነ በኢትዮጵያ ህዝብ በጀትና ሃብት እራሷን ችላ እንድትገነጠል የተደረገችው የኤርትራ ዜጎች በነፃ ከሚሰጣቸው የትምህርት ዕድል ተጨማሪ መሆኑ ነው ማለት ነው፡፡ ይህ ደግሞ የራሷ እያረረባት የሰው ታማስላለች ዓይነት መሆኑ አይቀሬ ነው፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት 250 ሜጋ ዋት በነፃ የመብራት ኃይል ለኤርትራ ለመስጠት እንደ ድርድር መነሻ አንስቶታል ስለተባለው ጉዳይ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲን ጠይቀናቸው “ውሸት ነው፣ የኢትዮጵያ መንግስት እንዲህ ዓይነት ሐሳብ አላቀረበም” ሲሉ ምላሽ ሰጥተውናል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ እና በየከተሞቹ ያለምንም ቅድመ ማስጠንቀቂያ ደስንገት እየጠፋ ስላለው የመብራት መጥፋት እንዲሁም ለጅቡቲና ሱዳን

ተሸጧል ስለተባለው የመብራት ኃይል ጉዳይ ምላሽ እንዲሰጡን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ወደሆኑት አቶ ምስክር ነጋሽ ጋር ብንደውልም በተደጋጋሚ ስብሰባ ላይ ነኝ በማለታቸው ምላሻቸውን ማግኘት አልቻልንም፡፡መንግስት ለኃይል ማመንጫ ግድቦች መስፋፋት የሚያደርገውን ጥረት እሰየው ከዚህ በተሻለ ይቀጥል እያልን አሉ በሙባሉ እና ከላይ በተነሱ ችግሮች ዙሪያ የኮርፖሬሽኑ ኃላፊዎችም ሆኑ ሌላ የሚመለከተው አካል ምላሽ ለመስጠት ቢፈልግ የዝግጅት ክፍሉ ለማቅረብ ዝግጁ መሆኑን ለመግለፅ እንወዳለን፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች በተደጋጋሚ ድንገት የመብራት መጥፋት በንብረትም ሆነ በዕለታዊ እንቅስቃሴዎች ላይ እየፈጠረ ያለውን ችግር ምንነት እስካሁን ከሚመለከተው አካል የተሰጠ ምላሽ ባለመኖሩ በኃይል አቅርቦትና አገልግሎት ላይ ነገ ምን ሊከሰት እንደ ሚችል ለመተንበይም ሆነ ለመዘጋጀት አስቸጋሪ አድርጎታል፡፡ እዚህ ላይ ኮርፖሬሽኑም ሆነ ሌላ የሚመለከተው የመንግስት አካል ከወዲሁ ለደንበኞቻቸው የቅድመ ማስጠንቀቂያም ይሁን የእርምት ምላሽ ሊሰጡ እንደሚገባ መጠቆም እወዳለሁ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ መንግስት የመብራት ኃይልን ለውጭ ምንዛሪ መሸጥ እንኳ ቢፈልግ ቅድሚያ የሀገር ውስጥ ፍጆታን በአግባቡ መሸፈን ያለበት ይመስለኛል፡፡