የኢትዮጵያ አየር ኃይል አብራሪዎች የጦር ሄሊኮፕተር ይዘው ስርዓቱን መክዳታቸውን መንግሥት አመነ

helicopterባለፈው አርብ ታህሣሥ 10 ቀን 2007 ዓ.ም. ከድሬዳዋ የአየር ኃይል ምድብ የጦር ልምምድ ላይ የነበሩት የኢትዮጵያ  የአየር ኃይል አብራሪዎች እና አንድ መካኒክ በስልጣን ላይ ያለውን ስርዓት በመክዳት ኤም አይ-35 የሆኑ ሁለት ዘመናዊ የጦር ሄሊኮፕተሮችን ይዘው ኤርትራ መግባታቸው ተረጋገጠ፡፡ ይሄንንም የኢትዮጵያ መንግስት መከላከያ ሚኒስቴር ዛሬ ታህሣሥ 13 ቀን 2007 ዓ.ም. ማመኑን የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ዘግቧል፡፡ አብሪዎቹ  ሻምበል ሳሙኤል ግደይ፣ መቶ አለቃ ቢልልኝ ደሳለኝ እና የሄሊኮፕተሩ ቴክኒሻን ፀጋብርሃን ግደይ መሆናቸውን መረጃዎች አመልክተዋል፡፡

አብራሪዎቹ ይዘዋቸው የጠፉት የጦር ሄሊኮፕተሮች የአንዱ  ዋጋ 36 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር  የሚገመት ሲሆን፤በኢትዮጵ  ከ720 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሆነ ይገመታል፡፡ እንደ ኢሳት ዘገባ ከሆነ የአርብ ዕለቱን ጨምሮ ባለፉት 6 ወራት  ውስጥ ብቻ 11 የመከላከያ ሚኒስቴር የአየር ኃይል አብራሪዎችና ባለሟሎች ከድተው ስርዓቱን በኃይል ለመጣል ወደ ሚታገሉ ታጣቂዎች መቀላቀላቸው ተጠቁሟል፡፡

Leave a comment