ዶ/ር መረራ ጉዲና ያቀረቡት የዋስትና መብት ጥያቄ ውድቅ ተደረገባቸው
(አዲስ ሚዲያ) ባለፈው የካቲት 24 ቀን 2009 ዓ. ም. በነበረው ቀጠሮ ዶ/ር መረራ ጉዲና በጠበቃቸው አማካኝነት የዋስትና መብታቸው እንዲከበር ጥያቄ አቅርበው ነበር። በዚህም ምክንያት የካቲት 30 ቀን 2009 ዓ. ም. አቃቤ ህግ ባቀረበው የዋስትና ጥያቄ ላይ ያለውን ተቃውሞ አቅርቦ፤ ለመጋቢት 1 ቀን 2009 ዓ. ም. ተይዞ የነበረው ቀጠሮ በዋስትናው ጉዳይ ላይ መርምሮ ብይን ለመስጠት ነበር።

ዶ/ር መረራ ጉዲና
ዳኞች በሁለቱም ወገን የቀረበውን ክርክር መመርመራቸውን ገልፀዋል፥ የዋስትና መብት በህገ መንግስቱ የተደነገገ ቢሆንም ፍፁም መብት ሳይሆን በህግ አግባብ ሊገደብ የሚችል እንደሆነ ጠቅሰው ዶ/ር መረራ ያቀረቡትን የዋስትና ጥያቄ ከዚህ አግባብ መታየት ያለበት ጉዳይ እንደሆነ ተናግረዋል።
ዳኞች በማስከተልም የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ስነ-ስርዐት አንቀፅ 63 ንዑስ አንቀፅ 1 ላይ “ማንኛውም የተያዘ ሰው የተከሰሰበት ወንጀል የሞት ቅጣትን ወይም አስራ አምስት አመት ወይም በላይ የሆነ ፅኑ እስራት የማያስቀጣ ከሆነ እና ወንጀል የተፈፀመበት ሰው በደረሰበት ጉዳት የማይሞት የሆነ እንደ ሆነ ፍርድ ቤቱ የዋስትና ወረቀት አስፈርሞ መልቀቅ ይችላል፡፡” እንደሚል ጠቅሰው፤ ዶ/ር መረራ ላይ የቀረበባቸው የመጀመሪያ ክስ (ወንጀለኛ መቅጫ አንቀፅ 32፣ 38 እና 238) የሚያስቀጣው የእድሜ ልክ እስራት ወይም የሞት ቅጣት በመሆኑ የዋስትና መብት እንደማይፈቀድላቸው ገልፀው ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ሆነው ክሳቸውን እንዲከታተሉ አዘዋል።
ዶ/ር መረራም የዋስትና መብት እንዳልተፈቀደላቸው ከሰሙ በኋላ
“1ኛ.ከእነ ጄኔራል መንግስቱ ንዋይና ጄኔራል ታደሰ ብሩ ዘመን ጀምሮ ከአንድ ትውልድ በላይ ገዳዮችን፣ ሟቾች፣ አሳሪዎችና ታሳሪዎች በበዙበት የሃገራችን የፓለቲካ አላማ ውስጥ በመቆየት አንድ ከሆዱ በላይ ለሃገሩ የሚያስብ ምሁር ማድረግ እንዳለበት ሁሉ ከአርባ አምስት ዓመታት በላይ ለሃገሬ የተሻለ ለውጥ እንዲመጣ መታገሌ እየታወቀ ወደ ጎን መገፋቱ ፤
2ኛ. ለሁላችንም የምትሆንና በእኩልነት የምታስተናግደን፣ ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ እንድትፈጠር ነፃ የፍትህ ስርአት በሃገራችን እንዲሰፍን ላለፉት 25 አመታት በመታገሌ፤ መከሰሴ አንሶ የሃገሪቱ ፓርላማ አባል ጭምር የነበርኩ ሰው ለተራ ወንጀለኛ የሚፈቅድ የዋስ መብት በመከልከሌ የተሰማኝ ጥልቅ ሃዘን ለራሴ ብቻ ሳይሆን እኛም ሆነ ልጆቻችን በሰላም ይኖሩበታል ለምንለው መከረኛ ሃገራችን አላልፍለት ብሎ ሲታመስ ለሚኖረው መከረኛ ህዝባችን ጭምር መሆኑን እንዲታወቅልኝ ነው።” ሲሉ ተናግረዋል።
በመጨረሻም በክሱ ላይ የሚቀርብ መቃወሚያ ለመቀበል ለሚያዚያ 16 ቀን 2009 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል። የተቀሩት ተከሳሾችን በተመለከተ በጋዜጣ እንዲወጣ የታዘዘው የጥሪ ማስታወቂያን ለማየት ለመጋቢት 29 ቀን 2009 ዓ. ም. የተያዘው ቀጠሮ እንደተጠበቀ መሆኑን በመግለፅ በዕለቱም ዶ/ር መረራ መቅረብ እንዳለባቸው ፍርድ ቤቱ ሲናገር ተደምጧል።
Ethiopia’s Cruel Con Game
David Steinman
In what could be an important test of the Trump Administration’s attitude toward foreign aid, the new United Nations Secretary-General, António Guterres, and UN aid chief Stephen O’Brien have called on the international community to give the Ethiopian government another $948 million to assist a reported 5.6 million people facing starvation.

Speaking in the Ethiopian capital, Addis Ababa, during the recent 28th Summit of the African Union, Guterres described Ethiopia as a “pillar of stability” in the tumultuous Horn of Africa, praised its government for an effective response to last year’s climate change-induced drought that left nearly 20 million people needing food assistance, and asked the world to show “total solidarity” with the regime.
Ethiopia is aflame with rebellions against its unpopular dictatorship, which tried to cover up the extent of last year’s famine. But even if the secretary general’s encouraging narrative were true, it still begs the question: Why, despite ever-increasing amounts of foreign support, can’t this nation of 100 million clever, enterprising people feed itself? Other resource-poor countries facing difficult environmental challenges manage to do so.
Two numbers tell the story in a nutshell:
1. The amount of American financial aid received by Ethiopia’s government since it took power: $30 billion.
2. The amount stolen by Ethiopia’s leaders since it took power: $30 billion.
The latter figure is based on the UN’s own 2015 report on Illicit Financial Outflows by a panel chaired by former South African President Thabo Mbeki and another from Global Financial Integrity, an American think tank. These document $2-3 billion—an amount roughly equaling Ethiopia’s annual foreign aid and investment—being drained from the country every year, mostly through over- and under-invoicing of imports and exports.
Ethiopia’s far-left economy is centrally controlled by a small ruling clique that has grown fantastically wealthy. Only they could be responsible for this enormous crime. In other words, the same Ethiopian leadership that’s begging the world for yet another billion for its hungry people is stealing several times that amount every year.
Read more… https://www.forbes.com/sites/realspin/2017/03/03/ethiopias-cruel-con-game/#586e691729d0
Source: Forbes
ዶክተር መረራ ጉዲና እና ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ክስ ተመሰረተባቸው
(አዲስ ሚዲያ) ከ3 ወር በፊት በአውሮፓ ፓርላማ ስለ ኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳይ ላይ ተጋብዘው ንግግር ያደረጉት ዶ/ር መረራ ጉዲና ወደ ሀገር ቤት ሲመለሱ ከአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ተይዘው ለ 3 ወራት በማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ከታሰሩ በኃላ የካቲት 16 ቀን 2009 ዓ።ም በገዥው መንግሥት ጠቅላይ አቃቤ ህግ አማካኝነት በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት ክስ ተመሰረተባቸው።

ዶክተር መረራ ጉዲና እና ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
የቀድሞ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስ መምህር የነበሩት እና የኦፌኮ ሊቀመንበር እንዲሁም የመድረክ ምክትል ሊቀመንበር የሆኑት ዶክተር መረራ ክስ የተመሰረተባቸው፥ በአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ንግግር ለማድረግ ተጋብዘው ሲመለሱ የአርበኞች ግንቦት ሰባት አመራር እና ሊቀመንበር ከሆኑት ከፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ጋር ታይተዋል በሚል እንደነበር ይታወቃል።
በዶ/ር መረራ ስም የተከፈተው በዚሁ የክስ መዝገብ ፥ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ሁለተኛ ተከሳሽ ፣ አቶ ጃዋር መሃመድ ሶስተኛ ተከሳሽ በመሆን በልይሉበት ክስ ተመስርቶባቸዋል፡፡ ሶስቱም ተከሳሾች የተከሰሱት በወንጀለኛ መቅጫ ህጉን የተለያዩ አንቀጾች በመተላለፍ ሲሆን አራተኛ እና አምስተኛ ተከሳሽ የሆኑት የኢትዮጵያ ሳተላይ ቴሌቪዥን ( ኢሳት) እና ኦሮሞ ሚዲያ ኔትወርክ ( ኢኤም ኤን) ሲሆኑ፥ ተቋማቱ የፀረ ሽብር ህጉን በመተላለፍ ተከሰዋል፡፡
ዶ/ር መረራ ሌላ ተጨማሪ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን መተላፍ በሚል ክስ ተመስቶባቸዋል፡፡ የክሱ ጭብጥም ተከሳሾች በዋና አድራጊነት ሽብር ተግባር መፈጸማቸውን እና ለኦሮሚያ እና አማራ ክልል አመጾች ማነሳሳት እና ንብረት መውደም ተጠያቂ መሆናቸው በክሱ ላይ ተጠቅሷል።
የፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤትም ክሱን ለማየት ለየካቲት 24 ቀን 2009 ዓ ም ቀነ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
በተለይ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከዚህ በፊት በሌሉበት በነ ጄነራል ተፈራ ማሞ የክስ መዝገብ የሞት ፍርድ የተፈረደባቸው ሲሆን፥ በነ አቶ አንዱዓለም አራጌ የክስ መዝገብ ደግሞ የዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት የተፈረደባቸው ሲሆን፥ የአሁኑ ከነ ዶ/ር መረራ ጉዲና ጋር የተመሰረተባቸው ክስ ለሶስተኛ ጊዜ መሆኑ ታውቋል።
መንግሥት ከህዳር 2008 ዓ ም ጀምሮ በተለይ በኦሮሚያ ፥ በአማራ ክልል እና በደቡብ ክልል ኮንሶ ከአንድ ዓመት በላይ የዘለቀ ህዝባዊ አመፅን ተከትሎ በርካታ ሰላማዊ ሰዎች በመንግሥት ወታደራዊ ኃይል ሲገደሉ፥ በአስር ሺህዎች የሚቆጠሩ ሲታሰሩ ከ15 ሺህ ያላነሱ በተለያየ ጊዜ ከእስር መልቀቁን መንግሥስት ቢያስታውቅም አሁንም ድረስ ህዝባዊ አመፁን ተከትሎ የታሰሩና ሰብዓዊ መብቶቻቸው እየተጣሰ ያሉ ዜጎች መንግሥስት ከእስር ልቅቄያቸዋለሁ ክሚለው ቁጥር እንደሚልቅ ይግመታል።
ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በፊት መንግሥት በጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ አማካኝነት ለህዝባዊ አምፁ ተጠያቂ ራሱ መንግሥት እና አመራሮች እንደሆኑ ቢይሳውቁም፥ ለግድያ፥ እስርና እንግልት የተዳረጉት ግን ሰላማዊ ዜጎች መሆናቸውን የሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች መግለፃቸው ይታወሳል።
ምርጫ ቦርድ በሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ውዝግብ ላይ ውሳኔውን አሳወቀ
ታምሩ ጽጌ
– ‹‹የምርጫ ቦርድ አካሄድ የተለመደ በመሆኑ የሚያስደንቅ አይደለም›› ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት
– ‹‹በፓርቲው አባላት መካከል ምንም ዓይነት ልዩነት የለም›› አቶ የሺዋስ አሰፋ

ላለፉት አራት ወራት ‹‹የሰማያዊ ፓርቲ ሕጋዊ መሪ (ሊቀመንበር) እኔ ነኝ እኔ ነኝ›› በማለት ሲወዛገቡ በከረሙት ኢንጂነር ይልቃል ጌትነትና አቶ የሺዋስ አሰፋ ላይ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የካቲት 8 ቀን 2009 ዓ.ም. ውሳኔውን አሳወቀ፡፡
ቦርዱ ውሳኔውን ያስታወቀው የሰማያዊ ፓርቲ መተዳደሪያ ደንብ አንቀጽ 10(6)ን በመጥቀስ፣ እነ አቶ የሺዋስ አሰፋ መስከረም 28 ቀን 2009 ዓ.ም. በፓርቲው ኦዲትና ምርመራ ኮሚሽን በኩል፣ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባዔ በመጥራት ምርጫ ማካሄዱንና አቶ የሺዋስን ሊቀመንበር አድርጎ መምረጡን ያሳወቀበትን ሪፖርት መርምሮ ነው፡፡
ከላይ የተጠቀሰው የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ አንቀጽ እንደሚያስረዳው፣ የፓርቲው ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የተሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ አልተወጣም ብሎ ካመነ፣ ብሔራዊ ምክር ቤቱ የመተማመኛ ድምፅ ሊሰጥ ይችላል፡፡ ነገር ግን ብሔራዊ ምክር ቤቱ የመተማመኛ ድምፅ ከነፈገው፣ በኦዲትና ምርመራ ኮሚሽን በኩል አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባዔ በመጥራት ችግሩ እንዲፈታ ማድረግ እንደሚችል ያብራራል፡፡ በመሆኑም ቦርዱ እነ አቶ የሺዋስ ያደረጉት የምርጫ ሒደትን ሲመረምር፣ በሕጉና በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት መፈጸማቸውን በማረጋገጥ መስከረም 28 ቀን 2009 ዓ.ም. የተደረገው ጠቅላላ ጉባዔ፣ በቦርዱ ተቀባይነት ያገኘ መሆኑን፣ በቦርዱ ጸሐፊና የጽሕፈት ቤቱ ዋና ኃላፊ በአቶ ነጋ ዱፊሳ ፊርማ ወጪ የተደረገው ደብዳቤ ያሳያል፡፡
ምርጫ ወይም ጠቅላላ ጉባዔው የተደረገው ኮረም ሳይሟላ፣ ታዛቢዎች በሌሉበትና የፓርቲውን መተዳደሪያ ደንብ ተጥሶ መሆኑን በመጥቀስ የፓርቲው ሕጋዊ ሊቀመንበር መሆናቸውን በመግለጽ ሲከራከሩ ስለነበሩት ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት ቦርዱ በውሳኔው ላይ ያለው ነገር የለም፡፡
ቦርዱ በውሳኔው እሳቸውን አስመልክቶ ምንም አለማለቱን አስመልክቶ ሪፖርተር ያነጋገራቸው ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት እንደተናገሩት፣ የምርጫ ቦርድ አካሄድ የተለመደ ነው፡፡ ‹‹አንድና ሁለት በመቶ ያህል ተስፋ ያደረግነው ሕዝቡን አስበው እውነተኛ ውሳኔ ይሰጣል የሚል ነበር፡፡ በመሆኑም የሚያስደንቅ አይደለም፡፡ እኛ የመጀመሪያ ሳንሆን በቅንጀት፣ በኦብኮ፣ በአንድነትና በመኢአድ ላይ የተፈጸመው በእኛም ላይ በመድረሱ አያስገርመንም፤›› ብለዋል፡፡
የመሠረቱት ፓርቲ እንደ ሌሎቹ ፓርቲዎች በሁለትና በሦስት አባላት መቀለጃ ሆኖ እንዳይቀጥል በሕግ ወይም ጠቅላላ ጉባዔው በሚወስነው ሁኔታ ለመታገል፣ የካቲት 11 እና 12 ቀን 2009 ዓ.ም. በሚያደርጉት ስብሰባ ለሕዝብ እንደሚያሳውቁ አስረድተዋል፡፡
የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ውሳኔ ተከትሎ ሰማያዊ ፓርቲ ዓርብ የካቲት 10 ቀን 2009 ዓ.ም. በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳስታወቀው፣ 15 ቀናት በማይፈጅ የውሳኔ ሐሳብ ከአራት ወራት በላይ ቦርዱ ሳያሳውቅ በመቅረቱ አላስፈላጊ ውጣ ውረዶች መከሰታቸውን አዲሱ የፓርቲው ሊቀመንበር አቶ የሺዋስ ተናግረዋል፡፡ ቦርዱ ዘግይቶም ቢሆን የሰጠው ውሳኔ ሰማያዊ ፓርቲ መተዳደሪያ ደንቡንና የፓርቲዎች የምርጫ ሕግን በማክበር የሚሠራ መሆኑን ያረጋገጠ በመሆኑ፣ ‹‹የቀድሞ አመራሮችና አንዳንድ አባላት እየፈጠሩት በነበረው ሁከት ግራ ለተጋቡ ደጋፊዎቻችን ጥሩ ምላሽ ነው፤›› ብለዋል፡፡
በፓርቲው ውስጥ መከፋፈል ስለነበር አባላትና ደጋፊዎች ግራ ተጋብተው መክረማቸውንና በፓርቲው ህልውና ላይ መተማመኛ ስለመኖሩ የተጠየቁት አቶ የሺዋስ፣ በፓርቲው ውስጥ መከፋፈል ያለ ለማስመሰል መሞከሩን አስረድተዋል፡፡ ነገር ግን አራቱም አካላት ማለትም ጠቅላላ ጉባዔው፣ ብሔራዊ ምክር ቤቱ፣ ሥራ አስፈጻሚውና የኦዲትና ምርመራ ኮሚሽኑ በሙሉ እንዳሉ መሆናቸውን አክለዋል፡፡
በሁሉም ክልሎችና በአዲስ አበባ ከተማ ያሉ በፓርቲ አባላት መካከል ምንም ዓይነት ክፍተትም ሆነ ልዩነት እንደሌለ አቶ የሺዋስ ገልጸዋል፡፡
ሌላው አቶ የሺዋስ የተናገሩት በገዢው ፓርቲና 22 ተቃዋሚ ፓርቲዎች ያደረጉትን ድርድር በሚመለከት ነው፡፡
በተለያዩ የመገናኛ ብዙኃንና የኅብረተሰብ ክፍሎች ‹‹ውይይትና ክርክር›› እየተደረገ እንደሆነ የሚናገሩት ስህተት መሆኑን የገለጹት አቶ የሺዋስ፣ ኢሕአዴግና ተቃዋሚ ፓርቲዎች አሁን እየተዘጋጁ ያሉት ‹‹ድርድር›› ለማድረግ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ውይይት የሚዲያ ተግባር ሲሆን፣ ክርክር ደግሞ በምርጫ ወቅት የሚደረግ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ‹‹በእርግጥ ድርድር በሁለት ወገኖች መካከል የሚደረግ ቢሆንም እኛ ግን 22 ሆነን ጀምረነዋል፤›› ብለዋል፡፡
ከ2002 ዓ.ም. ጀምሮ በገዢው ፓርቲና በተቃዋሚዎች መካከል ድርድር ተደርጎ እንደነበር ያስታወሱት አቶ የሺዋስ፣ አንድም ጊዜ የተገኘ ውጤት እንደሌለና አሁንም የተለየ ውጤት ይገኛል የሚል እምነት እንደሌላቸው ተናግረዋል፡፡
ኢሕአዴግን ሁሉም ፓርቲዎች ለድርድር ያልጠየቁበት ጊዜ እንዳልነበርና ምንም ምላሽ ሰጥቶ እንደማያውቅ ያስታወሱት አቶ የሺዋስ፣ የሕዝብ ጥያቄ አይሎ ሲነሳ ግን በሩን መክፈቱን አስረድተዋል፡፡ የመደራደርን ሐሳብ በቅድሚያ ያነሱት የአገሪቱን ሁኔታ የተመለከቱ አቅጣጫው ያስፈራቸው የውጭና የአገር ውስጥ ሽማግሌዎች ሆነው ሳለ፣ ኢሕአዴግ ግን ሐሳቡን ራሱ እንዳመነጨው በማድረግ ‹‹እንደራደር›› ማለቱ ተገቢ አለመሆኑንና ዕውቅናውን ለአገር ሽማግሌዎች መስጠት እንዳለበትም አስረድተዋል፡፡ ኢሕአዴግ እንደ አንድ ፓርቲ መደራደር እንጂ ሰብሳቢ፣ ታዛቢም ሆነ አደራዳሪ ሊሆን እንደማይችልም አክለዋል፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ እውነተኛ ድርድር ለማድረግና ሕዝቡ በድርድሩ እምነት እንዲያድርበት በቅድሚያ የፖለቲካና የህሊና እስረኞችን መፍታት፣ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ማንሳት፣ ድርድሩን የኢትዮጵያ ጉዳይ ያገባኛል ያሉ ወገኖች ሁሉ እንዲሳተፉ ክፍት ማድረግና ለግልም ሆነ ለሕዝብ መገናኛ ብዙኃን ክፍት መሆን እንዳለበት እምነቱ መሆኑን እንደገለጸ አቶ የሺዋስ አብራርተዋል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲን ያህል አባላት የታሰሩበት አንድም ተቃዋሚ ፓርቲ እንደሌለም ገልጸው፣ ድርድሩ ከመጀመሩ በፊት ሊፈቱ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
ሁሉም ፓርቲዎች ኢሕአዴግን ጨምሮ የሕዝብን ጥያቄ በሚመልስ መንገድ ድርድር ማድረግ እንዳለባቸው ያስታወቁት አቶ የሺዋስ ሕዝቦች ባነሱት ጥያቄ ምክንያት የሞቱ፣ የተፈናቀሉ፣ ወጥተው የቀሩ፣ የታሰሩ ለምሳሌ ዶ/ር መራራ ጉዲና፣ ሁለት ጋዜጠኞች ኤልያስ ገብሩና አናንያ ሶሪ ሌሎችም መፈታት እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡ ድርድሩ ሙሉ የሚሆነውም ይኼ በተግባር ከተፈተጸመ እንደሆነም አክለዋል፡፡
አሁን ገና ድርድር እንዳልተጀመረና በቀረቡት አጀንዳዎችም ላይ መስማማት እንዳልተቻለ የገለጹት አቶ የሺዋስ፣ አደራዳሪ ማን ይሁን? ታዛቢ ማን ይሁን? የአጀንዳዎች ቅደም ተከተል እንዴት ይሁን? እና ድርድሩ ለየትኛው ሚዲያ ክፍት ይሁን? የሚለው ጥያቄ የካቲት 8 ቀን 2009 ዓ.ም. ምላሽ ሊያገኝ ባለመቻሉ እሳቸውን ጨምሮ ሰባት አባላት ያሉበት ኮሚቴ ተመርጦ፣ የተጠጋጋ ሐሳብ እንዲያቀርብ ለየካቲት 17 ቀን 2009 ዓ.ም. ቀጠሮ መያዙን አሳውቀዋል፡፡
ውጤታማ ድርድር ለማድረግና የፖለቲካ ለውጥ ለማምጣት የሕዝብ፣ የተፎካካሪ ፓርቲዎችና በተቃውሞ ጎራ በያለበት ተሠልፈው የሚገኙ አካላትንና የመንግሥትን ፈቃደኝነት ማግኘት አስፈላጊ መሆኑን አቶ የሺዋስ አስረድተዋል፡፡ ዘገባው የሪፖርተር ነው።
በቂሊንጦ ለደረሰው ቃጠሎ ተጠያቂዎች ናችሁ በሚል በሽብር የተከሰሱት እስረኞች ላይ የሚደርሰው ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት ቀጥሏል
*ለፍርድ ቤት አቤቱታ ማሰማታቸውን ተከትሎ ጨለማ ቤት እንዲታሰሩ ተደርገዋል

ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ ፎቶ ከሲውድን ሬዲዮ
ነሐሴ 28 ቀን 2008 ዓ.ም በአዲስ አበባ ቂሊንጦ እስር ቤት የደረሰውን የእሳት ቃጠሎ ተከትሎ ለጠፋው የሰው ህይወትና ለደረሰው የንብረት ውድመት ተጠያቂዎች ናችሁ በሚል የፌደራል አቃቤ ህግ በፍይደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት የሽብር ክስ መስርቶባቸው በእስር ላይ የሚገኙት 38 ተከሳሾች ላይ የሚፈጸምባቸው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ቀጥሏል፡፡
ተከሳሾች ታህሳስ 14 ቀን 2009 ዓ.ም በነበረው የችሎት ውሎ ወቅት በእስር ቤት እየደረሰብን ነው ያሉትን ኢ-ሰብዓዊ አያያዝ በተመለከተ አቤቱታ ማሰማታቸውን ተከትሎ ወደ እስር ቤቱ ሲመለሱ ጨለማ ክፍል፣ በጠባብ ቤት ውስጥ ታጭቀው እንዲታሰሩ መደረጋቸውንም ለማወቅ ተችሏል፡፡
በህክምና ላይ የሚገኙት የ66 ዓመቱ ኢትዮ- ሲውድናዊው የልብ ህክምና ባለሙያ እና የ “አዲስ የልብ ህክምና ሆስፒታል” መስራች ዶ/ር ፍቅሩ ማሩን ጨምሮ በእነ ማስረሻ ሰጤ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ የቀረበባቸው 38 ተከሳሾች፣ የጸረ-ሽብር ህጉን አንቀጽ 3 (1፣ 2፣ 4 እና 6) ስር የተመለከተውን የወንጀል ድርጊት ተላልፈዋል በሚል አቃቤ ህግ በህዳር 13 ቀን 2009 ዓ.ም በይፋ ክስ እንደመሰረተባቸው ይታወሳል፡፡ ከዚህ ክስ በተጨማሪም ሌሎች 131 ሰዎች ላይ በተመሳሳይ ክስ መከፈቱ ለመንግስት ቅርበት ባላቸው መገናኛ ብዙሃን ተዘግቦም ነበር፡፡
ተከሳሾቹ በምርመራ ወቅት እጅግ የከፋ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ይፈጸምባቸው እንደነበር በተደጋጋሚ ይፋ መደረጉ የሚታወስ ሲሆን፣ ይህንኑ የተፈጸመባቸውን ድርጊት ለችሎት ለማስረዳት መሞከራቸውን ተከትሎ ደግሞ አሁን ላይ በጨለማ ክፍል እንዲታሰሩ ተደርገዋል፡፡
በታህሳስ 14 ቀን 2009 ዓ.ም በነበረው የችሎት ውሎ ዳኞቹ ወደ ችሎት ሲገቡ ሁሉም ተከሳሾች ከመቀመጫቸው በመነሳት፣ ‹‹በእሳት ቃጠሎው ወቅት ህይወታቸውን ላጡ በእስር ላይ የነበሩ ወንድሞቻችን የህሊና ጸሎት እናደርጋለን›› በማለት ጸሎት አድርገው መቀመጣቸውና በወቅቱ ለደረሰው ቃጠሎም ተጠያቂው ያሰራቸው አካል መሆኑን መናገራቸው አሁን ላይ በጨለማ ክፍል ለመታጎር እንደዳረጋቸው ቤተሰቦቻቸው እምነታቸውን ይገልጻሉ፡፡
የተከሳሽ ቤተሰቦች በተከሳሾች ላይ እየደረሰ ያለው ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት እንዲቆም የከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንትን ቢያነጋግሩም፣ ‹‹ጉዳያችሁን ወደ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ውሰዱ›› የሚል መልስ እንዳገኙ ታውቋል፡፡ በዚህም የተከሳሽ ቤተሰቦች ጠቅላይ አቃቤ ህግ በማምራት ዋና ጠቅላይ አቃቤ ህግ አቶ ጌታቸው አምባየንና ምክትል ዋና ጠቅላይ አቃቤ ህግ አቶ ብርሃኑ ወ/አገኝን አነጋግረዋል፡፡ አቶ ጌታቸው ለተከሳሽ ቤተሰቦች ‹‹ጉዳያችሁን በጽሁፍ አቅርቡ›› በማለት አቤቱታቸውን በጽሁፍ የተቀበሉ ሲሆን፣ በጉዳዩ ላይ ታህሳስ 21 ቀን 2009 ዓ.ም ምላሽ ለመስጠት ቀጠሮ ሰጥተው ነበር ፡፡ ነገር ግን ከቀናት በኋላም ፍርድ ቤቱ ውሳኔ የሚሰጥበት ጉዳይ ነው የሚል ሰበብ ምላሽ እንዳላገኙ ተናግረዋል፡፡
ለፍርድ ቤቱ የቀረበው የተከሳሾችን አቤቱታ ከታች ይመልከቱ


ምንጭ፦ ኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ፕሮጀክት