Tag Archives: Ethiopia

በቂሊንጦ ለደረሰው ቃጠሎ ተጠያቂዎች ናችሁ በሚል በሽብር የተከሰሱት እስረኞች ላይ የሚደርሰው ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት ቀጥሏል

*ለፍርድ ቤት አቤቱታ ማሰማታቸውን ተከትሎ ጨለማ ቤት እንዲታሰሩ ተደርገዋል

dr-fikru-maru

ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ         ፎቶ  ከሲውድን ሬዲዮ

ነሐሴ 28 ቀን 2008 ዓ.ም በአዲስ አበባ ቂሊንጦ እስር ቤት የደረሰውን የእሳት ቃጠሎ ተከትሎ ለጠፋው የሰው ህይወትና ለደረሰው የንብረት ውድመት ተጠያቂዎች ናችሁ በሚል የፌደራል አቃቤ ህግ በፍይደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት የሽብር ክስ መስርቶባቸው በእስር ላይ የሚገኙት 38 ተከሳሾች ላይ የሚፈጸምባቸው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ቀጥሏል፡፡

ተከሳሾች ታህሳስ 14 ቀን 2009 ዓ.ም በነበረው የችሎት ውሎ ወቅት በእስር ቤት እየደረሰብን ነው ያሉትን ኢ-ሰብዓዊ አያያዝ በተመለከተ አቤቱታ ማሰማታቸውን ተከትሎ ወደ እስር ቤቱ ሲመለሱ ጨለማ ክፍል፣ በጠባብ ቤት ውስጥ ታጭቀው እንዲታሰሩ መደረጋቸውንም ለማወቅ ተችሏል፡፡

በህክምና ላይ የሚገኙት የ66 ዓመቱ ኢትዮ- ሲውድናዊው የልብ ህክምና ባለሙያ እና የ “አዲስ የልብ ህክምና ሆስፒታል” መስራች ዶ/ር ፍቅሩ ማሩን ጨምሮ በእነ ማስረሻ ሰጤ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ የቀረበባቸው 38 ተከሳሾች፣ የጸረ-ሽብር ህጉን አንቀጽ 3 (1፣ 2፣ 4 እና 6) ስር የተመለከተውን የወንጀል ድርጊት ተላልፈዋል በሚል አቃቤ ህግ በህዳር 13 ቀን 2009 ዓ.ም በይፋ ክስ እንደመሰረተባቸው ይታወሳል፡፡ ከዚህ ክስ በተጨማሪም ሌሎች 131 ሰዎች ላይ በተመሳሳይ ክስ መከፈቱ ለመንግስት ቅርበት ባላቸው መገናኛ ብዙሃን ተዘግቦም ነበር፡፡

ተከሳሾቹ በምርመራ ወቅት እጅግ የከፋ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ይፈጸምባቸው እንደነበር በተደጋጋሚ ይፋ መደረጉ የሚታወስ ሲሆን፣ ይህንኑ የተፈጸመባቸውን ድርጊት ለችሎት ለማስረዳት መሞከራቸውን ተከትሎ ደግሞ አሁን ላይ በጨለማ ክፍል እንዲታሰሩ ተደርገዋል፡፡

በታህሳስ 14 ቀን 2009 ዓ.ም በነበረው የችሎት ውሎ ዳኞቹ ወደ ችሎት ሲገቡ ሁሉም ተከሳሾች ከመቀመጫቸው በመነሳት፣ ‹‹በእሳት ቃጠሎው ወቅት ህይወታቸውን ላጡ በእስር ላይ የነበሩ ወንድሞቻችን የህሊና ጸሎት እናደርጋለን›› በማለት ጸሎት አድርገው መቀመጣቸውና በወቅቱ ለደረሰው ቃጠሎም ተጠያቂው ያሰራቸው አካል መሆኑን መናገራቸው አሁን ላይ በጨለማ ክፍል ለመታጎር እንደዳረጋቸው ቤተሰቦቻቸው እምነታቸውን ይገልጻሉ፡፡

የተከሳሽ ቤተሰቦች በተከሳሾች ላይ እየደረሰ ያለው ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት እንዲቆም የከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንትን ቢያነጋግሩም፣ ‹‹ጉዳያችሁን ወደ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ውሰዱ›› የሚል መልስ እንዳገኙ ታውቋል፡፡ በዚህም የተከሳሽ ቤተሰቦች ጠቅላይ አቃቤ ህግ በማምራት ዋና ጠቅላይ አቃቤ ህግ አቶ ጌታቸው አምባየንና ምክትል ዋና ጠቅላይ አቃቤ ህግ አቶ ብርሃኑ ወ/አገኝን አነጋግረዋል፡፡ አቶ ጌታቸው ለተከሳሽ ቤተሰቦች ‹‹ጉዳያችሁን በጽሁፍ አቅርቡ›› በማለት አቤቱታቸውን በጽሁፍ የተቀበሉ ሲሆን፣ በጉዳዩ ላይ ታህሳስ 21 ቀን 2009 ዓ.ም ምላሽ ለመስጠት ቀጠሮ ሰጥተው ነበር ፡፡ ነገር ግን ከቀናት በኋላም ፍርድ ቤቱ ውሳኔ የሚሰጥበት ጉዳይ ነው የሚል ሰበብ ምላሽ እንዳላገኙ ተናግረዋል፡፡

ለፍርድ ቤቱ የቀረበው የተከሳሾችን አቤቱታ  ከታች ይመልከቱ

%e1%8b%a8%e1%89%b0%e1%8a%a8%e1%88%b3%e1%88%be%e1%89%bd-%e1%8a%a0%e1%89%a4%e1%89%b1%e1%89%b3

%e1%8b%a8%e1%89%b0%e1%8a%a8%e1%88%b3%e1%88%be%e1%89%bd-%e1%8a%a0%e1%89%a4%e1%89%b1%e1%89%b3-2

ምንጭ፦ ኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ፕሮጀክት

ኢትዮጵያ- የአማራ ህዝብ የመብት ጥያቄና ( #AmharaProtests) በመንግስት የተወሰደው የኃይል እርምጃ

በአማራ የተቃውሞ ድምጽ በሚያሰሙ ዜጎች ላይ የሚደርሰው የመብት ጥሰት ግድያ፣ የእስርና ደብዛ መጥፋት መጠኑ ይለያይ እንጂ አሁንም እንደቀጠለ ነው፡፡ በተለይም አስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ተከትሎ አሁንም ድረስ በጎንደር፣ በባህር ዳርና በምዕራብ ጎጃም ዞኖች ዜጎችን በገፍ የማሰሩ እርምጃ ቀጥሏል፡፡

nigist-yirga-gonder-on-public-protest

ወጣት ንግስት ይርጋ  በጎንደር ህዝባዊ ተቃውሞ ላይ

በተቃውሞ ሰልፎች የተሳተፉ ወጣቶችን በተለያዩ ፖሊስ ጣቢያዎች በገፍ ማሰሩ ተቃውሞዎች በበረቱባቸው ከተሞች ከፍተኛ ነው ፡፡ ለምሳሌ በጎንደር ከተማ በሚገኙ 1ኛ፣ 2ኛ፣ 3ኛ፣ 4ኛ፣ 5ኛ እና 6ኛ ፖሊስ ጣቢያዎች በጠባብ ክፍሎች ውስጥ በአንድ ጣቢያ በአማካይ እስከ 140 ሰዎች እንደሚታሰሩ ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡

ጎንደር ከተማ ውስጥ 5ኛ ፖሊስ ጣቢያ ለሁለት ሳምንታት ታስሮ የነበረ ወጣት ደረጀ ጌቱ (ስሙ የተቀየረ) እንደሚናገረው በጣቢያው ውስጥ አብረውት ታስረው የነበሩት አብዛኞቹ ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ ላይ መሳተፋችሁ በፎቶ ተረጋግጧል በሚል ለእስር ተዳርገው የነበሩ ናቸው፡፡

በተመሳሳይ በባህር ዳር ከተማ በሚገኙ ፖሊስ ጣቢያዎች እንዲሁ በከተማዋ ተደርጎ በነበረው ሰላማዊ ሰልፍ ወቅት በተሳተፉ ወጣቶች በገፍ እየታሰሩ ነው፡፡ እነዚህ ወጣቶች አንዳንዶቹ በአጭር ጊዜ ሲታሰሩ እና ሲፈቱ ሌሎች ደግሞ በተደጋጋሚ መታርና መፈተታ እንደሚገጥማቸው ማየት ተችሏል፡፡
በእነዚህ ፖሊስ ጣቢያዎች የሚታሰሩትን ማን እንደታሰረና፣ የት እንደታሰረ ቤተሰብና ዘመድ የማወቅ እድል ቢኖረውም ሌሎች የት እንደታሰሩ ሳይታወቅ ለቀናት፣ ለሳምንታትና ለወራትም የሚከርሙ መኖራቸውም ታውቋል፡፡ እነዚህ የእስር ስፍራዎች በይፋ የማይታወቁና በተቃውሞ እንቅስቃሴው እጃቸው በሰፊው አለበት በሚል መንግስት የጠረጠራቸውን “የሚመረምርባቸው” ናቸው፡፡

ከእነዚህ ድብቅ የእስር ቦታዎች መካከል ለምሳሌ ባህር ዳር አባይ ማዶ ከብአዴን ጽ/ቤት ጀርባ የሚገኝ ቀድሞ የመሳሪያ መጋዘን የነበረ ስፍራ ይገኝበታል፡፡ በዚህ ቦታ የሚታጎሩ ወጣቶችን ቤተሰቦቻቸው ለመጠየቅም ሆነ በዚያ ስፍራ ስለመኖር አለመኖራቸው ለማወቅ እንደማይችሉ ታስረው የተፈቱና፣ ታስረው እንደነበርም እንዳይናገሩ ማስፈራሪያ ደርሷቸው የወጡ ይመሰክራሉ፡፡ አበበ አስረስ (ስሙ የተቀየረ) በዚህ ድብቅ የእስር ቦታ ለ17 ቀናት ሲሰቃይ ቆይቶ መለቀቁን ይናገራል፡፡

‹‹ቦታው የሆነ መጋዘን ነገር ነው፤ ሰፊ አዳራሽ ነው፡፡ በዚህ አዳራሽ ውስጥ በጣም ብዙ ሰዎች አብረውኝ ታስረው ነበር፡፡ የእስራችን ምክንያት ብለው የነገሩን ባህር ዳር ነሐሴ 01/2008 ዓ.ም በነበረው ሰላማዊ ሰልፍ ወቅት ሰልፉን አደራጅታችኋል የሚል ነው፡፡ በእስራችን ጊዜ ቤተሰቦቻችን አንድም ቀን አላገኙንም፡፡ በኋላ ብዙዎችን ወደ ብርሸለቆ ሲወስዷቸው እኔን ድጋሜ ሰልፍ ላይ ካገኘንህ እንገድልሃለን ብለው ዝተውብኝ የሆነ ወረቀት ላይ አስፈርመው ለቀውኛል፡፡ ማታ ላይ ነው በመኪና ከሌሎች ሦስት ልጆች ጋር ጥለውኝ የሄዱት›› ሲል ያስታውሳል አበበ፡፡

አበበ አስረስ ከድብቅ እስር ቤቱ መፈታቱን ተከትሎ ዘመድ ለመጠየቅ በሚል ከአካባቢው ዞር ለማለት አስቦ የቤተሰቦቹን ምክር ተቀብሎ ወደ አዲስ አበባ ዘመድ ጋር ሳምንታትን አሳልፏል፡፡ ‹‹በጣም ከባድ ጊዜ ነበር እስር ላይ ሆኜ ያሳለፍኩት›› የሚለው አበበ፣ ከሳምንታት የአዲስ አበባ ቆይታ በኋላ የገና በዓልን ከቤተሰቦቹ ጋር ለማሳለፍ ወደ ባህር ዳር በተመለሰበት ወቅት፣ ‹‹የት ጠፍተህ ከርመህ እንደመጣህ እናውቃለን!›› በሚል በድጋሜ ለእስር እንደተዳረገ ታውቋል፡፡

በድብቅ እስር ቤቶችም ሆነ በፖሊስ ጣቢያዎች የሚታሰሩ ሰዎች የከፋ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንደሚፈጸም ለማረጋገጥ የተቻለ ሲሆን፣ በተለይ ድብደባ በብዙዎቹ ላይ በምርመራ ወቅት የሚፈጸም የሰብአዊ መብት ጥሰት ነው፡፡ በባህር ዳር ከተማ 9ኛ ፖሊስ ጣቢያ የሚታሰሩ የፖለቲካ እስረኞች በምርመራ ወቅት ጥፍርን እስከመንቀል የሚደርስ ኢ-ሰብዓዊ የሆነ ድርጊት ይፈጸምባቸዋል፡፡

ብዙዎች በፖሊስ ጣቢያ ለሳምንታት እንዲቆዩ ከተደረገ በኋላ ወደ ብርሸለቆ የወታደራዊ ማሰልጠኛ ተቋም ለ‹ተሃድሶ ስልጠኛ› ተግዘዋል፡፡ በማሰልጠኛ ተቋሙ በሚኖራቸው ቆይታም ቢሆን ተመሳሳይ፣ አንዳንዴም የከፋ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ይፈጸምባቸዋል፡፡ (በተሃድሶ ማሰልጠኛ ስፍራዎች ስለሚፈጸም የሰብዓዊ መብት ጥሰት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ፕሮጀክት በቅርቡ ለማሳያነት ይፋ ያደረገውን ሪፖርት መመልከት ይቻላል፡፡)
በአማራ ክልል የተቀሰቀሰውን ህዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ መንግስት በዋናነት ቀድሞውንም በሰላማዊና ህጋዊ መንገድ በሚታገሉ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ላይ ያነጣጠረ የእስር እርምጃ ሲወስድ ታይቷል፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት ‹የጸረ-ሽብር ግብረ-ኃይል› በሽብር ጠርጥሬያቸዋለሁ በሚል 2008 ዓ.ም ሐምሌ ወር መግቢያ ላይ በጎንደር በነበሩ የወልቃይት አማራ ማንነት ጠያቂ የህዝብ ተወካይ (ኮሚቴ) አባላትን ለማሰር በተደረገ እንቅስቃሴ በሁዋላ በአማራ ክልል የተለያዩ ዞኖች ህዝባዊ ተቃውሞዎች በተደጋጋሚ መከሰታቸው ይታወሳል፡፡ የህዝባዊ ተቃውሞዎቹም መነሻ ከመስፋፋታቸው በፊት ጎንደር ላይ ብዙ ነዋሪዎች የተሳተፉበት ትልቅ እና ሰላማዊ ሰልፍም ተካሄዷል፡፡

ከጎንደር በማስከተል በሐምሌ 29 ቀን 2008 ዓ.ም የተከናወነው የባህር ዳር ሰልፍ ግን በተለየ መልኩ በአሳዝኝ ሁኔታ የተጠናቀቀ ነበር፡፡ ሰልፉ ሲጀምር ሰላማዊ የነበር ቢሆንም ዘግይቶ የመንግስት ታጣቂዎች በወሰዱት እርምጃ በአንድ ቀን ብቻ ከ50 በላይ የሚገመቱ ንጹሃን መገደላቸው የሚታወስ ነው፡፡

እስካሁን ባለው መረጃ መሰረት አማራ ክልል ከሚገኙት በአጠቃላይ 11 ዞኖች በስድስቱ ዞኖች የጎላ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ተደርጎባቸዋል፡፡ እነዚህም ሰሜን ጎንደር፣ ደቡብ ጎንደር፣ ባህር ዳር ልዩ ዞን፣ አዊ ዞን፣ ምዕራብ ጎጃም እና ምስራቅ ጎጃም ዞኖች ናቸው፡፡ በስድስቱ ዞኖች የሚገኙ አብዛኞቹ የዞንና የወረዳ ከተሞች (አንዳንድ ቦታዎች ላይ ገጠር ቀበሌዎችንም ጨምሮ) መንግስትን የሚቃወሙ ሰላማዊ ሰልፎችንና የቤት ውስጥ አድማዎችን አስተናግደዋል፡፡ የሰሜን ጎንደር ዞን ዋና ከተማና የቱሪስት መናሃሪያዋ ጎንደር ላይ የተጀመረው እንቅስቃሴ፣ ደባርቅ፣ ደብረታቦር፣ መተማ፣ አምባ ጊዮርጊስ፣ ወረታ፣ ስማዳ፣ ጋይንት፣ ባህር ዳር፣ ፍኖተ ሰላም፣ ቡሬ፣ እንጅባራ፣ ዳንግላ፣ ቻግኒ፣ ቲሊሊ፣ ብርሸለቆ፣ ቋሪት፣ ደምበጫ፣ አማኑኤል፣ ደብረ ማርቆስና ሌሎች በርካታ ከተሞችን አዳርሷል፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት አድማሱን እያሰፋ የሄደውን የተቃውሞ እንቅስቃሴ ለመግታት የኃይል እርምጃ መውሰዱን በተግባር ከማሳየቱም በላይ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ የመንግስት ጦር ተቃውሞውን ለመግታት ‹ማንኛውንም እርምጃ እንዲወስድ› ማዘዛቸው የሚታወስ ነው፡፡ በዚህም በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተገድለዋል፡፡ በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች እንደ ብርሸለቆ የመሰሉ የጦር ማሰልጠኛዎች ውስጥ ሳይቀር በተለያዩ ቦታዎች ታስረዋል፤ በርካቶች ደግሞ የደረሱበት አልታወቀም፡፡ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ፕሮጀክት ባለፉት ወራት በተደረጉት የአማራ ህዝብ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች ወቅት ለጊዜው ያሰባሰበው መረጃም ብዙ ዜጎች በመንግስት ኃይሎች እንደተገደሉ ያሳያል፡፡ ከዚህ በታች ያለው ዝርዝር ለጊዜው ተለይተው የታወቁ የሟቾችን ስምና አድራሻ አካትቶ ለማሳያነት የቀረበ ነው፡፡

የተገደሉ ሰዎች ስም አድራሻ
1. ይሻል ከበደ ……………………………ጎንደር
2. ሲሳይ ታከለ ……………………………ጎንደር
3. አበበ ገረመው…………………………ባህር ዳር
4. ተፈሪ ባዬ ………………………………ባህር ዳር
5. እድሜዓለም ዘውዱ ……………………ባህር ዳር
6. አደራጀው ደሳለኝ …………………… ባህር ዳር (ዩኒቨርሲቲ)
7. ይበልጣል…………………………………ደብረ ታቦር
8. ግዛቸው ከተማ …………………………ጎንደር
9. አዳነ አየነው ………………………………ጎንደር
10. ማንደፍሮ አስረስ………………………ባህር ዳር
11. ቁምላቸው ቃሉ …………………………ባህር ዳር
12. አወቀ ጥበቡ ……………………………ፍኖተ ሰላም
13. ሲሳይ ከበደ ……………………………ጎንደር
14. ሰጠኝ …………………………………ጎንደር (የወልቃይት ተወላጅ)
15. እቴነሽ ሽፈራው ……………………ም/ጎጃም፣ ጂጋ
16. እንዳለው መኮነን …………………ጎንድር፣ ጋይንት
17. እሸቴ ……………………………… ባህር ዳር (ቀበሌ 16)
18. ሰለሞን አስቻለ ………………………ባህር ዳር
19. ሙሉቀን ተፈራ ………………………ባህር ዳር
20. አደራጀው ኃይሉ ………………………ባህር ዳር
21. አስማማው በየነ ……………………… ባህር ዳር
22. ታዘበው ጫኔ …………………………ባህር ዳር
23. አስራት ካሳሁን …………………………ባህር ዳር
24. የሺዋስ ወርቁ ……………………………ባህር ዳር
25. ብርሃን አቡሃይ ………………………… ባህር ዳር
26. ሽመልስ ታየ ………………………………ባህር ዳር
27. አዛናው ማሙ …………………………… ባህር ዳር
28. ሲሳይ አማረ ………………………………ባህር ዳር
29. ሞላልኝ አታላይ ………………………… ባህር ዳር
30. መሳፍንት ………………………………………ጎንደር፣ እስቴ
31. እንግዳው ዘሩ ………………………………… ባህር ዳር
32. ዝናው ተሰማ ………………………………… ባህር ዳር
33. ሞገስ ሞላ ………………………………………ባህር ዳር
34. ሞላልኝ ታደሰ …………………………………ባህር ዳር
35. ይታያል ካሴ ………………………………………ባህር ዳር
36. እሸቴ ብርቁ …………………………………… ባህር ዳር
37. ሞገስ………………………………………………ባህር ዳር
38. ገረመው አበባው ………………………………ባህር ዳር
39. ማህሌት…….…………………………………… ባህር ዳር
40. ተስፋየ ብርሃኑ …………………………………ባህር ዳር
41. ፈንታሁን………………………………………… ባህር ዳር
42. ሰጠኝ ካሴ ……………………………………… ባህር ዳር
43. ባበይ ግርማ ………………………………………ባህር ዳር
44. አለበል ዓይናለም ……………………………… ደብረ ማርቆስ
45. አብዮት ዘሪሁን …………………………………ባህር ዳር
46. አበጀ ተዘራ ………………………………………ወረታ
47. ደሞዜ ዘለቀ ……………………………………ወረታ
48. አለበል ሀይማኖት ………………………………ባህር ዳር
49. እስቲበል አስረስ …………………………………አዴት
50. ዓይናዲስ ለዓለም ……………………………… ደብረወርቅ
51. ሽመልስ ወንድሙ ……………………………… ቡሬ
52. ታደሰ ዘመኑ ………………………………………አዴት
53. ሀብታሙ ታምራት ……………………………ባህር ዳር
54. ይበልጣል እውነቱ …………………………ባህር ዳር፣ ጭስ አባይ
55. ይህነው ሽመልስ ………………………………ደብረታቦር
56. በለጠ ካሴ ………………………………………ደብረታቦር
57. አዳነ እንየው ……………………………………ጎንደር፣ ቀበሌ 16
58. አለማየሁ ይበልጣል ……………………………ዳንግላ
59. ያየህ በላቸው …………………………………… ዳንግላ
60. በረከት አለማየሁ …………………………………ዳንግላ
61. ተመስገን ……………………………………………ዳንግላ
62. ቅዱስ ሀብታሙ ………………………………… ባህር ዳር
63. ፍስሃ ጥላሁን ………………………………………ባህር ዳር
64. ሰለሞን ጥበቡ …………………………………… ቻግኒ
65. እስቲበል አስረስ …………………………………አዴት
66. ዘሪሁን ገደብዬ …………………………………ጎንደር
67. ሲሳይ ባብል ………………………………………ጎንደር
68. ባየሁ ጎንደር ………………………………………ጎንደር
69. በለጡ መሃመድ …………………………………አዘዞ፣ ጎንደር
70. እንጀራ ባዬ ………………………………………አዘዞ፣ ጎንደር
71. ወንድም ……………………………………………ጎንደር
72. ግርማቸው ከተማ ………………………… ላይ አርማጭሆ
73. ሊሻን ከበደ ………………………………………አይባ
74. መሌ አይምባ …………………………………… አይባ
75. አዛነው ደሴ ………………………………………አርማጭሆ
76. አራገው መለስ ……………………………………አርማጭሆ
77. ሰጠኝ አድማሱ ……………………………………ደልጊ
78. ታረቀኝ ተሾመ ……………………………………ደልጊ
79. ሄኖክ አታሎ ………………………………………ደልጊ
80. ደሴ ደረሰ …………………………………………ሻውራ
81. ግርማቸው ሞገስ …………………………………ሻውራ
82. ወርቁ ጠቁሳ ………………………………………ሻውራ
83. ማማዬ አንጋው …………………………………ዳንሻ
84. ፈንታ አህመድ ……………………………………ዳንሻ
85. ክንፌ ቸኮል ………………………………………በአከር
86. ሲሳይ ታከለ ……………………………………… አርማጭሆ
87. ማዕረግ ብርሃን …………………………………ደብረታቦር
88. መምህር ተስፋየ ብርሃን ……………… ደብረታቦር ቀበሌ 01
89. ይበልጣል ደሴ ………………………… ደብረታቦር ቀበሌ 01
90. አራጋው መለሰ …………………………… አርማጭሆ
91. አዳነ አያሌው ………………………… አርማጭሆ
92. አያናው ደሴ ………………………… አርማጭሆ
93. ትርፌ አጣናው ……………………… አርማጭሆ
94. መምህር ብርሃኑ አየለ …………… ሰሜን ሸዋ፣ ማጀቴ
95. አብራራው አለማየሁ ………………ደቡብ ጎንደር፣ ስማዳ
96. ተመስገን ሲሳይ …………………… ደቡብ ጎንደር፣ ስማዳ
97. ጋሻው ሲራጅ ……………………… ደቡብ ጎንደር፣ ስማዳ
98. ፈንታ ሞገስ ……………………… ደቡብ ጎንደር፣ ስማዳ
99. ታደለ ያየህ ……………………………ምዕራብ ጎጃም፣ ቡሬ

(*ማስታወሻ፡- መንግስት ህዝባዊ ተቃውሞዎች በበረቱባቸው አካባቢዎች የኢንተርኔትና የስልክ ግንኙነቶችን በሙሉና በከፊል መዝጋቱ በእነዚህ አካባቢዎች ስለተከሰቱ ጉዳዮች መረጃ የማግኘት ስራውን አዳጋች በማድረጉ ይህ ዝርዝር ሁሉንም የመብት ጥሰት የደረሰባቸው ዜጎችን ያሳያል ተብሎ አይጠበቅም፡፡)

*ሌላው ከአማራ ህዝባዊ ተቃውሞ እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ ለእስር ተዳርገው የሽብር ክስ የተመሰረተባቸው
1. ንግስት ይርጋ………የመብት ተሟጋች፣ አድራሻ ሳንጃ ሰሜን ጎንደር…. ቃሊቲ እስር ቤት ታስራ ትገኛለች
2. አለምነው ዋሴ የመኢአድ አባል አድራሻ ጎንደር ቂሊንጦ በእስር ላይ ያለ
3. ቴዎድሮስ ተላይ……….አድራሻ ጎንደር
4. አወቀ አባተ……………….የመኢአድ አባል
5. በላይነህ አለምነህ…የሰማያዊ ፓርቲ አባል፣ አድራሻ ባህር ዳር
6. ያሬድ ግርማ…………………. የመኢአድ አባል
7. አታላይ ዛፌ…የወልቃይት አማራ ማንነት መብት ኮሚቴ አባል

*ክስ ሳይመሰረትባቸው በእስር ላይ የሚገኙ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት
7. ማሩ ዳኛው
8. ቢሆን
9. መልካሙ ታደለ
10. ሲሳይ ታፈረ
11. ወርቁ ጥላሁን
12. ድንቁ
13. ስማቸው ማዘንጊያ
14. እያዩ መጣ
15. ድርሳን ብርሃኔ
16. አንዳርጌ አባይ
17. ዮናስ ሰለሞን
18. መሃመድ ኑርየ
19. መምህር መሃመድ አሊ
20. መንግስቴ ብርሃኔ
21. ጌታነህ ደምሴ
22. ታደለ እንዳልፈራ
23. መምህር ለወየሁ ጌቱ
24. እሸቴ ደረሰ
25. ጌጤ ላሽተው
26. ሰይዒድ እንድሪስ
27. አህመድ በዛብህ
28. ጀማል ኡመር
29. አብደላ መሃመድ
30. አዲሱ ጌታነህ
31. ዘሪሁን እሸቱ
32. ጀማል ይመር
33. አበበ ጥላሁን
34. ተሻገር ወልደሚካኤል
35. እያሱ ሁሴን
36. በላቸው አወቀ
37. ዘውዱ ነጋ
38. ወልደመስቀል ማማየ
*የህዝቡን የመብት ጥያቄ (ህዝባዊ ተቃውሞ) ደግፋችኋል በሚል ከታሰሩት መካከል፡-
39. ገድፍ ጌታነህ……ሰሜን ጎንደር በለሳ ወረዳ
40. ሊቀሊቃውንት እዝራ (ቤተ-ክርስቲያንን ሽፋን አድርገው የህዝቡን ተቃውሞ ይደግፋሉ በሚል የታሰሩ)
41. ቀለመወርቅ ዓለሙ (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የጎንደር ሀገረ ስብከት ጳጳስ ኃላፊ)
42. ሂሪያኮስ አበበ…..ጎንደር ከተማ
43. ዶክተር ጋሹ ክንዱ
(ዶክተር ጋሹ ክንዱ የቡሬ ዳሞት ሆስፒታል ሜዲካል ዳሬክተር ናቸው፡፡ ታህሳስ 27 ቀን 2009 ዓ.ም ለገና በዓል ወደ ቤተሰቦቻቸው ባመሩበት ጊዜ ባህር ዳር ከተማ ለእስር ተዳርገው ወደ አዲስ አበባ ማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ እንዲዛወሩ ተደርገው በእስር ላይ ይገኛሉ፡፡

ምንጭ፦ ኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ፕሮጀክት (ኢሰመፕ) የተዘጋጀ

ARE WE SELLING THE NATION OUT?

kebour-ghenna

Kebour Ghenna

You won’t believe this….we hardly believe it ourselves… The Federal Democratic Republic of Ethiopia has put the Ethiopian Shipping Lines (ESL) S.C. on sale (apparently for minority stake…). Is the government so short of money to run its business and service its loans that it has to look for such a short cut? Or is this a matter of “privatization” or “economic efficiency”? By the way, I read that privatization increase neither efficiency nor competition, but do lead to price increases for consumers, higher costs for government, corruption, embezzlement and the destruction of democracy.
But this is a deeper subject …let me leave it for another day.

Now, how does one explain a situation where, one good morning, the Federal Government announces the sale of one its prized assets, which has taken almost three generations to build? Should we applaud the government for this daring move? Should we be grateful for its flair. No debate, no contest, no explaining to the public what other options were considered that could have avoided the sale of this national treasure. What’s more disappointing is the fact that policymakers, in the last couple of months, have been promising to be transparent, open, and inclusive but judging from events on the ground, we have not moved an inch in that direction.

Still believe in democracy?
Many years ago, 1964 G.C to be exact, Emperor Haile Selassie’s government established the ESL with two share holders: the government (49%) and a US firm (51%). In the late sixties the government bought back the 51% of the shares (with real money, if you know what I mean) owned by the US firm. Half a century later we’re back to square one. Selling our hard earned stake, this time to a Chinese company! The Emperor would have screamed!
This is not good news. It tells us there is far more problem in the horizon than potential upside.

From where I sit the proposal to sell the ESL is outrageous. It amounts to disinheritance of future Ethiopians. National assets like the ESL are strategic investments for not just economic but security reasons as well. I don’t know about you, but I can’t bear the idea that a Chinese company may soon control the ESL, and who knows, in a not too distant future many of the country’s public assets.

Not long ago the magazine African Business reported:
“In the next five years, the company (meaning ESL) will extend the entire transport and logistics chain, which could make it the largest liner trader in Africa in the next five years. It will extensively build its competitive advantage and outreach in the oil and gas shipment to serve the international market through strategic partnerships. Existing constraints in finance and limited access to foreign credit suppliers is a challenge. However, the company’s performance report shows a positive return that will attract credit suppliers to work with the company: its strict follow-up and implementation of international rules and regulations has enabled Ethiopia to be among the very few IMO white-listed countries.”

Local news outlets have also regularly reported on the profits of the ESL. You try to make out what is going on here.

Now, I really do not have anything against the sales of assets but then it should only be those that are either not profitable or you cannot run efficiently. As I said, my heart was made heavier when I noted the absence of any debate on the issue, and the news was reported as a benign matter of fact. Who can trust a government when its institutions that are meant to ensure economic prosperity and unity through sound policies fail to do so? Isn’t it this type of behavior that triggers more chaos and panic than poor governance? Apart from the economic dimension, how can we ignore that national assets such as the ESL are instruments of unity in a country that is plural like ours? Afar, Amhara, Gambela, Oromo, Somali, Tigray, Welayta and all other groups have the consciousness that national investments unite us, and that gains or otherwise there from are nationally shared.

No doubt the proposal to sale of the ESL makes many Ethiopians uneasy. From talking to ordinary people I get the sense that the ESL deal has made many compatriots uneasy for reasons they couldn’t quite articulate.

In fact I think the uneasiness of the people has more to do with what it says about the peculiar fiscal climate in the country. How is it that in one of the fastest growing nation on earth, the government simply don’t have the cash to maintain such a strategic asset, the political will to raise such funds, or the competence to run such reasonably profitable operations? Why is Ethiopia being forced to sell off long-term cash cows for short-term cash? People sense that the Chinese buyer would take the company and move it to Shanghai, or Hong Kong. I doubt if the contract spells out in detail obligations of the buyers to invest in maintenance or to maintain jobs opportunities for Ethiopians, or to keep a lid on shipping rates.

Remember selling a public asset is a classic one-shot – a short-term measure that bolsters the balance sheet today but that can’t be repeated. While politicians focus on getting through the next few fiscal years with minimum pain, foreign Chinese companies are thinking about how to get rich off of shipping business for the next three-quarters of a century.
Of course, by selling the ESL at high prices, Ethiopia could be taking foreigners for a ride. In the eighties the Japanese famously overpaid for Rockefeller Center in New York, after all. It’s possible that the FDRE just ripped off the Chinese on this deal. But I doubt it.

Ah!… Two more questions:
Think Ethiopian Airlines and Ethiopian Electric Power and ET Telecom are safe? Think again!
And who reaps the commission from the ESL deal?
You may have the same reaction we did: This is crazy!

ማንም ከኢትዮጵያዊነት ማማ ሊያወርደኝ አይችልም!

bedlu

በድሉ ዋቅጅራ

ሰሞኑን በፌስቡክ አድራሻዬ የጓዳ መልእክት ደረሰኝ፡፡ ‹‹አንተ በእርግጥ ማንነት አለህ? አንድ ጊዜ ኦሮሞነትህን ክደህ ጉራጌ ነኝ ትላለህ፡፡ ሌላ ጊዜ ኦሮሞ ነኝ ትላለህ፡፡ ያልገባህ ግን ጉራጌውም ሆነ ኦሮሞው ካንተ ሺህ ጊዜ የሚሻሉ ምሁራን አለው፡፡ አይፈልጉህም፡፡ የእንዳንተ አይነቱ መጠራቀሚያ ትምክህተኛ አማራ ስለሆነ እሱን ብትመርጥ ይሻልህ ነበር፡፡ . . . ›› ብሎ ይጀምርና ዋና ሀሳቡ ከዚህ ያልዘለለ አንድ አንቀጽ ይጨምራል፡፡

‹‹ሁሉም ነገር ለበጎ ነው›› እነሆ ታክቶኝ የተውኩትን ፌስቡክ እንድመለስበት አደረገኝ፡፡
ስለማንነት እኔ የማስበው እንዲህ ነው፡፡ . . . .
ትልቁ የራስ ማንነት መስፈሪያ የጎሳ ቁጭበሉ አይደለም፡፡ ሰው እንኳን ከጎሳው ከብሄራዊ መስፈሪያም የሚተርፍ ፍጡር ነው፡፡ የሰው ልጅ ነኝና ጉራጌነት ወይም ኦሮሞነት ሙሉ ማንነቴን አይገልጸውም፡፡ እንኳን ከጎሳ ከኢትጵያዊነትም ይተርፋል ማንነቴ፡፡ በኢሬቻ ላይ ስለሞቱት የምቆስለው ኦሮሞ ስለሆንኩ አይደለም፤ በቅርብ ጊዜ በአማራ ክልል በተፈጠረው ሁከት ስለተጎዱት አማራ ስላልሆንኩ የማይሰማኝ ከሆነ ሰብአዊ ፍጡር ነኝ አልልም፡፡ የሆነ የልቤ ጥግ ላይ በሶርያ ንጹሀን ላይ ስለሚደርሰው የሚደማ ክፍል አለ፡፡ ማንኛውም ሰው በአንድ ቋንቋ ተግባብቶ፣ አንድ የተለየ ባህል አዳብሮ በቋንቋውና በባህሉ ከመገለጹ አስቀድሞ ሰው በመሆኑ ይገለጽ ነበር፡፡ ፈጣሪም አዳም/አደም እና ሄዋን/ሀዋን ሲፈጥር ጎሳ ይቅርና ዜግነት አልነበራቸውም፡፡

ለእኔ ቋንቋዬ የሀሳብ መግለጫ፣ ባህሌ የአኗኗሬ መንገድ ብቻ ነው፡፡ እናቴ ጉራጌ ናት – ክስታኔ፡፡ አባቴና አባቱ ክስታንኛ አቀላጥፈው የሚናገሩትን ያህል ኦሮምኛም ይናገራሉ፡፡ በድሉ – ዋቅጅራ – ደበላ – ወልደጊዮርጊስ – ካሳ እያለ የሚዘልቀው የአባቴ ወገን መጠሪያ ሌሎችን የሚያስጨንቃቸውን፣ ግራ የሚያጋባቸውን ያህል እኔን አስጨንቆኝ አያውቅም፤ ግራም አያጋባኝም፡፡ የማያስጨንቀኝ እነሱን ስለምጠየፍ አይደለም፡፡ የማያስጨንቀኝ በማኛቸውም ማንነት ማንነቴን መበየን፣ ስለማልፈልግ ነው፡፡ እናቴ ኬርአለም ክስታኔ ናት፤ አባቴና አያቴ የኦሮሞና የጉራጌ ድብልቅ ሊሆኑ ይችላሉ፤ ወልደጊዮርጊስና ካሳ ትግሬ ወይም አማራ ሊሆኑም ላይሆኑም ይችላሉ፡፡ እኔ ውስጥ ያለው ግን ከነዚህ ሰዎች ጎሳ በላይ ነው፡፡ እኔ ውስጥ በደም ከዝርያዎቼ ከተቀበልኩት ይልቅ፣ ካደግኩበት የኦሮሞ ማህበረሰብ ከልጅነት እስከ ጉርምስና የቀሰምኩት ይበልጣል፡፡ በወጣትነቴ ባሌ ለሶስት አመታት፣ ጎንደርና ጎጃም ለአስር አመታት ስኖር ማንነታቸውን አትመውብኛል፡፡ ባህር ተሻግሬም አውሮፓ ላይ ያን ያህል ኖሬያለሁ፡፡ ታዲያ እንዴት ነው የእኔን ማንነት በእናትና አባቴ ጎሳ (ምንም ይሁን ምን) የሚገለጸው? አዎ የክስታኝና ቋንቋን አፌን ፈትቼበታለሁ፤ እርግጥ ነው በጉራጌና በኦሮሞ ባህል ከልደት እስከ ጉርምስና ጥሪት ቋጥሬበታለሁ፤ አንድም ቀን ግን እራሴን ጉራጌ ወይም ኦሮሞ ብዬው አላውቅም፡፡ ላለፉት ሀያ አምስት አመታት ማንነትን በጎሳ የመበየን ፖለቲካ ተንሰራፍቶ እንኳን ጎሳዬን የማንነቴ መበየኛ አድርጌው፣ ወይን ሆኖ ተሰምቶኝ አላውቅም፡፡ ለዚህ ነው ጉራጌ ወይም ኦሮሞ መሆን አለመሆኔ የማያስጨንቀኝ፡፡ እኔ ከዚያ የበለጠ ሳልሸራረፍ የሚገልጠኝ ማንነት አለኝ – ኢትዮጵያዊንት፡፡

በ1991 አ. ም. የውጭ ትምህርት እድል አገኘሁና ፓስፖርት አስፈለገኝ፡፡ ኢምግሬሽን መስሪያ ቤት ሄጄ እንዲሰጠኝ አመለከት፡፡ ለወራት ጠብቅ አሉኝ፡፡ እኔ ደግሞ በሳምንት ውስጥ መሄድ ነበረብኝ፡፡ ከአንዲት ሀላፊ ዘንድ አቀረቡኝና ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የተጻፈልኝን የተባበሩት ደብዳቤ አሳይቼ ጉዳዩን አስርዳሁ፡፡ ያን ጊዜ ከዛሬው የተሻሉ ሀላፊዎች ነበሩ፡፡ በሳስት ቀን እንደሚደርስ ነግራኝ እራስዋ ፎርሙን ትሞላልኝ ገባች፡፡ የተጠየቅሁትን ስመልስ ትጽፋለች፡፡ የባለቤቴን ዘር/ጎሳ ጠየቀችኝ፤ ‹‹አላውቅም›› ስላት፣ ልታምን አልቻለችም – በፍጹም፡፡ ‹‹የልጅህን እናት ማንነት አታውቅም›› ከተጋባን አመት ተመንፈቃችን ነበር፡፡ ጉዳዩ ከህሊናዋ በላይ እንደሆነ ሁኔታዋ ይናገራል፡፡ ‹‹ማንነትዋን አውቃለሁ፣ የማላውቀው ጎሳዋን ነው›› ስላት፣ ስምዋን ጠየቀችኝና ስነግራት፣ ‹‹አማራ›› ብላ ፎርሙ ላይ ሞላች፡፡ ወደባህር ዳር ስመለስ ባለቤቴን ብጠይቃት፣ የኦሮሞና የአማራ ድብልቅ ልትሆን እንደምትችል ነገረችኝ፤ እርግጠኛ ግን አልነበረችም፡፡ ይህን መናገሬ ጎሳን ለማንነት መገለጫ አድሬጌ አለመቀበሌ፣ የዛሬው የጎሳ ፖለቲካ የፈጠረብኝ የጎንዮሽ ጉዳት አለመሆኑን ለማሳየት ነው፡፡

የሀገሬ ሰው በጎሳ ተደራጅቶ ለሀገሩን ችግር መፍትሄ ለመስጠት ሲሞክር ማየት፣ በተለይ በዚህ ሉላፊነት እንደሰደድ እሳት እየተዛመተ ባለበት ክፍለ ዘመን፣ ከማሳዘን አልፎ ተስፋ የሚያስቆርጥ ነው፡፡ በተለይ በውጭ የሚኖረው ዲያስፖራ በጎሳ እየተደራጀ፣ ‹‹የዚህ ጎሳ ተጠሪ እኔ ነኝ አንተ አይደለህም›› እየተባባለ ሲራኮት ማየት፣ ለሀገራቸው ሁለንተናዊ ታሪክ፣ አሁን ላለችበት ሁኔታ ያላቸው አረዳድ በወቅቱ ፖለቲካዊ አስተሳሰብ ተኮርኩሮ የገነፈለ እንደሆነ ለመገመት ምርምር አይጠይቅም፡፡ ‹‹ኦሮሞዎች ተደራጅተን የኦሮሞን መብት እናስከብር፤ አማራዎች ተደራጅተን የአማራን መብት እናስከብር፤ ጉራጌዎች ተደራጅተን የጉራጌን መብት እናስከብር፤ . . . ወዘተ. ብሎ መነሳት፣ በእኛ ሀገር ነባራዊ ሁኔታ ዘለቄታዊ የህዝቦች መብት መከበርንና ሰላምን አያመጠም፡፡ እያንዳንዱ ጎሳ የራሱን መብት ማስከበርን ዋና አላማው አድርጎ ከተደራጀ፣ ከሰማንያ በላይ ጎሳዎች በሚኖሩባት ሀገር የህዝቦችን መብት ተከብሮ በሰላምና በፍቅር፣ በመተሳሰብ መኖር ያዳግታል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ የአማራ ወይም ኦሮሞ ህዝብ መብት ሊከበር የሚችለው፣ የሀገሪቱ ህዝቦች በሙሉ የእነሱ መብት መከበር እንዳለበት አምነው ለመብታቸው መከበር ከታገሉላቸው ብቻ ነው፡፡ አንዱ ህዝብ ለሁሉም ህዝቦች፣ ሁሉም ህዝቦች ለአንዱ ህዝብ መብት ከታገሉ ብቻ ነው የኢትዮጵያ ህዝቦች መብታቸው ተከብሮ አብረው በሰላምና በፍቅር የሚኖሩት፡፡

ጎሳዊ አስተሳሰብን የሀገራችን ችግሮች መፍቻ አድርጎ ማሰብ ገኖ የወጣው በዚህ ባለንበት ፖለቲካዊ አስተዳደር ነው፡፡ የሚገርመው ደግሞ ‹‹የሀገራችን ችግሮች ምንጭ ይህ ጎሳን መሰረት ያደረገ ፖለቲካዊ አስተሳሰብ ነው›› ብለው ተቃውመው የተነሱ ወገኖች እራሳቸው በጎሳ መደራጀታቸው ነው፤ ችግሩን የፈጠረውን አስተሳሰብ ህዳግ ተከትለን፣ አንድን ችግር ለመፍታት መነሳት የህልም ጉዞ ነው – እስከምንባንን እውን የሚመስል፡፡ ችግርን ለመፍታት የችግሩ ምንጭ ከሆነው አስተሳሰብ ማፈንገጥ ያሻል – ለአዲስ መፍትሄ በአዲስ መንገድ ማሰብ፡፡ ‹‹የእኔ ማንነት አዲስ የማንነት መገለጫ፣ ያልነበረ ነው›› ለማለት አይቃጣኝም፤ ግን ከወቅታዊው ጠባብ አስተሳሰብ ካሰፈነው የማንነት መገለጫ ያፈነገጠ ነው፡፡ ክስታንኛ ቋንቋዬ ነው፡፡ በክስታንኛና በኦሮምኛ ባህል ውስጥ አድጌያለሁ፡፡ ግን ሁለቱም ማንነቴን አይበይኑም፡፡ በቋንቋዬ ክስታኔ ስሆን፣ የኦሮሞ ባህሌ ይጎድላል፡፡ በባህሌ ኦሮሞ ስሆን፣ ቋንቋዬ ክስታንኛ ይጎድላል፡፡ እኔ ኢትዮጵያዊ ነኝ፡፡ ኢትዮጵያዊነቴ ውስጥ እንኳን ግዝፍ የነሳ ቋንቋና ባህሌ፣ ረቂቁ ህልምና ቅዠቴ አለ፡፡ ኢትዮጵያዊ ስሆን ሙሉ እሆናለሁ፡፡

ኢትዮጵያዊ ነኝ!

ኢትዮጵያዊ ነኝ!
በላሊበላ አስቀድሼ፣ ሸህ ሁሴን ባሌ የተገኘሁ፤
በአባ ገዳ ተመራርቄ፣ መካ ላይ እርዝቅ ያገኘሁ፡፡
ኢትጵያዊ ነኝ!!
ሳነቴ ላይ ውርጭና ጉም፣ ዳሽን ጫፍ ግግር በረዶ፤
ደሎ መና የአዋራ ጭስ፣ ዳሎል ላይ የእሳት እርጎ፡፡
ኢትጵያዊ ነኝ!!
ጎጥ አይበቃኝ – የሀገር ስፍር፤
ጎሳ አይገልጠኝ – የሰው ስእል፡፡
ኢትጵያዊ ነኝ!!

ኢትጵያዊ ነኝ!!
ይርጋለም ያጋጥኳትን ላም፣ ወለጋ ላይ አሰርሬ፤
ትኩስ እንገርዋን የጠጣሁ፣ አክሱም ላይ ጥገት አስሬ፤
ሰሜን ያለብኩትን ወተት፣ በአርሲ ጮጮ የሞላሁ፤
ጋምቤላ ወተቱን ንጬ፣ የሀረሪ ቆንጆ የቀባሁ፡፡
ወሰን የለሽ እግረ ፌንጣ፣
ሞተ ሲሉኝ ብን – ትር የምል፣ ሄደ ሲሉኝ የምመጣ፤
የቅዠት ምች፣ ህልም ፈቺ . . . ዳነ ሲሉኝ የማገረሽ፤
ወሰን አልባ እግረ ሞረሽ፡፡
ኢትጵያዊ ነኝ!!

ኢትጵያዊ ነኝ!!
ጃውሌ የደንጊያ እጣን፣ ከርቤ ከጊንር ቋጥሬ፤
አቦዳይ ጫት ተዘይሬ፤
ከጂማ አባጁፋር መንደር፣ ከአዎል – በረካ ጀባ፤
ሶዶ ዋዳ ተዘፍኖልኝ – ጎዴ ላይ ቃጢራ አድሬ፤
አፋር ላይ በግመል እንገር፣ ምርቃናዬን የሰበርኩ፤
የሀገሬን ባንዲራ፣ ለአፋር ግመል ማተብ ያሰርኩ፡፡
ወሰን የለሽ እግረ ፌንጣ፣
ሞተ ሲሉኝ ብን – ትር የምል፣ ሄደ ሲሉኝ የምመጣ፤
የቅዠት ምች፣ ህልም ፈቺ . . . ዳነ ሲሉኝ የማገረሽ፤
ወሰን አልባ እግረ ሞረሽ፡፡
ኢትጵያዊ ነኝ!!

የመብት አራማጅ ንግስት ይርጋ የሽብር ክስ ተመሰረተባት

በአማራ ክልል የተቀሰቀሰውን ህዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ ጎንድር ውስጥ ለእስር ተዳርጋ ወደ ማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ተዛውራ ከአራት ወራት በላይ ያሳለፈችው አክቲቪስት ንግስት ይርጋና ሌሎች አምስት ሰዎች የሽብር ክስ ተመስርቶባቸዋል፡፡

nigest-yirga_amhara_resitance

ንግስት ይርጋ

የፌደራል አቃቤ ህግ ታህሳስ 28 ቀን 2009 ዓ.ም. በጻፈውና ለተከሳሾች ጥር 1 ቀን 2009 ዓ.ም. እንዲደርሳቸው በተደረገው የክስ ቻርጅ ላይ እንደተመለከተው ንግስት ይርጋ ‹‹ከአርበኞች ግንቦት ሰባት የሽብር ድርጅት ጋር ግንኙነት በመፍጠር፣ በሰሜን ጎንደርና በሌሎች የአማራ ክልል አካባቢዎች አመጽ በማስነሳት፣ አመጹን በበላይነት በመምራትና በማስቀጠል…›› የሽብር ወንጀል ድርጊት ተሳታፊ በመሆን ክስ ቀርቦባታል፡፡

ንግስት ይርጋ 1ኛ ተከሳሽ በተደረገችበት የክስ ዝርዝር ላይ እንደተመለከተው፣ ተከሳሾች በ2001 ዓ.ም የወጣውን የጸረ ሽብር አዋጅ አንቀጽ 3/4/6ን በመተላለፍ ተከሰዋል፡፡

የመብት አራማጅ ንግስት ይርጋ ነሐሴ ወር ላይ በጎንደር ከተማ በነበረው ሰላማዊ ሰልፍ ወቅት ‹‹የአማራ ህዝብ አሸባሪ አይደለም›› የሚል ጽሁፍ የሰፈረበት ቲሸርት ለብሳ በሰልፉ ላይ መታየቷ ይታወሳል፡፡

ክሱ የቀረበለት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት የቀረበውን ክስ በንባብ ለማሰማት ለጥር 10 ቀን 2009 ዓ.ም ቀጠሮ ይዟል፡፡
ምንጭ፦ EHRP