በአዲስ አበባ ኮልፌ የሚገኙ የአባት ጡረተኛ አርበኞች መኖሪያቸው እንዲፈርስ ተደረገ

Ethiopian elders patrioties

በአዲስ አበባ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 09 እና 10 ውስጥ ከኃይለስላሴ ዘመን ጀምሮ በቀድሞ መንግስት በተሰጣቸው ካምፕ ውስጥ ሲኖሩ የነበሩ ከ500 በላይ የአባት ጡረተኛ አርበኞች ቤታቸው በመንግስት እንዲፈርስ በመደረጉ ከነቤተሰቦቻቸው ሜዳ ላይ መበተናቸውን ገለፁ፡፡

በተለምዶ ኮልፌ ልኳንዳ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኘውንና ከጥንት ጀምሮ የአባት ጡረተኞችና የአርበኞች መኖሪያ የሆነውን የወታደር ካምፕ ቦታው ተከልሎላቸው የሰሩት ራሳቸው አርበኞቹ መሆናቸውን ነዋሪዎቹ የገለፁ ሲሆን፤ ፈጽሞ ባላሰቡበትና ባልተዘጋጁበት ሁኔታ መኖሪያ ካምፓቸው ያለ ምንም ተለዋጪ ማረፊያ መሳሪያ በታጠቁ ወታደሮች እንዲፈርስ መደረጉ እንዳስደነገጣቸው  መናገራቸውን የኢሳት ዘገባ አመልክቷል፡፡  ነዋሪዎቹ  ውሳኔውን በመቃወም እስከ ፍትህ ሚኒስቴር ድረስ አቤቱታ ቢያቀርቡም  ሰሚ እንዳላገኙ ተጠቁሟል።

ካምፕ የሚገነው ቤታቸው ፈርሶ ሜዳ ላይ ከተበተኑትና የላስቲክ ድንኳን ሰርተው ከተጠለሉት ነዋሪዎች መካከል የኤች አይ ቪ/ ኤድስ ህመምተኞችና በርካታ ህጻናት እንደሚገኙበት ኢሳት በዘገባው አስታውሷል። የአካባቢው መስተዳድር አካላት ነዋሪውን ሊያነጋግሩ ሲመጡ የአርበኞቹ  ልጆች ባንዲራ እያውለበለቡ አባቶቻቸው በሞቱላትና ወደነሱ ባስተላለፉዋት ሀገራቸው የመኖር መብት ሊነፈጉ እንደማይገባና ያለ አማራጭ መኖሪያ ሜዳ ላይ መውደቅ እንደሌለባቸው አቤቱታ ቢያቀርቡም፤ የመስተዳድሩ አካላት ወጣቶቹ ባንዲራ በመያዛቸው ቁጣቸውን በመግለፅ ያለምንም መፍትሔ መመለሳቸውን ነዋሪዎቹ በሀዘን መናገራቸው ተጠቁሟል። አሁንም ነዋሪው የመንግስት ያለህ፣ያገር ያለህ እያለ ተማፅኖውን እያሰማ እንደሚገኝ የጥር 7 ቀን 2007 ዓ.ም.የኢሳት ዘገባ አመልክቷል።

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: