Police Brutally Attack Peaceful Protesters in Addis Ababa ahead of National Election
By Betre Yacob
Police brutally attacked and dispersed peaceful demonstrators in the capital Addis Ababa on Sunday as they try to protest against the ongoing government repression on opposition political parties and dissents in run-up to the countries general election..
Political activists say the Sunday’s attack against the peaceful demonstrators is further evidence of the authorities’ determination to clamp down the activities of opposition political parties ahead the election.
In this latest brutal attack against peaceful protesters, dozens of members and supporters of Unity for Democracy and Justice Party (UDJ) were seriously injured. The incident is the most blatant and massive case of lethal police brutality in Ethiopia.
According to reports, demonstrators were brutally beaten with baton, stick and iron rod in the head, face, hands, and legs. One of the victims is said to have been a pregnant woman. Reports show the victims were taken to hospital right away, and some…
View original post 506 more words
አዲስ አበባ በሚገኝ ትምህርት ቤት አጥር በመደርመሱ ከተጎዱት መካከል የአንዲት ተማሪ ህይወት አለፈ
ባለፈው ሳምንት በአዲስ አበባ ሳሪስ አካባቢ በሚገኘው ፍሬህይወት አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አጠገብ ከባቡር መንገድ ስራ ጋር በተያያዘ በተደረገ ቁፋሮ የትምህርት ቤቱ አጥር ተደርምሶ 11 ተማሪዎች ላይ ጉዳት አድርሶ የነበረ ሲሆን፤ ከተጎዱት መካከል ተማሪ ፅዮን ንጉሴ ሆስፒታል ውስጥ የህክምና ዕርዳታ እየተደረገላት በደረሰባት ከባድ ጉዳት ምክንያት ህይወቷ ማለፉ ተሰምቷል፡፡ የተማሪ ፅዮን ንጉሴ የቀብር ስነስርዓትም ዛሬ ሳሪስ አካባቢ በሚገኘው ብሔረ ፅጌ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን መፈፀሙን የደረሰን መረጃ አመልክቷል፡፡
የትምህርት ቤቱ አጥር የተደረመሰው ቻይናዎች ጥንቃቄ በጎደለው መልኩ አጥሩ ጥግ ቁፋሮ በሚያደርጉበት ወቅት ተማሪዎች ዕረፍት ላይ ስለነበሩ አንዳንዶቹ ሲጫወቱ ሌሎች ደግሞ በአጥሩ ጥቅ ሲያጠኑ አደጋው መድረሱን በወቅቱ የነበሩ የዓይን እማኞች ተናግራዋል፡፡ በወቅቱ በቻይናዎቹ ድርጊት የተበሳጩ ተማሪዎቹ ቁጣቸውን ሲገልፁ በስፍራው በነበሩ ቻይናዎችና የአዲስ አበባ ፖሊሶች በርካታ ተማሪዎች መደብደባቸውም ተጠቁሟል፡፡ ስለተፈጠረው አደጋም ሆነ ስለተማሪዎቹ ጉዳት የመንግስት አካላት እስካሁን ምንም ያሉት ነገር የለም፡፡
ሁለት ታዋቂ የአውሮፓ ኩባንያዎች በኦሞ ሸለቆ ጥጥ የተሠሩ ምርቶች አንገዛም አሉ
ዮሐንስ አንበርብር
ታዋቂዎቹ የአውሮፓ ጨርቃ ጨርቅ ኩባንያዎች የጀርመኑ ቼቦና የስዊድኑ ኤችኤንድኤም በኢትዮጵያ ኦሞ ሸለቆ ውስጥ የተመረተ የጥጥ ምርትን የሚጠቀም የጨርቃ ጨርቅ ምርቶች እንደማይገዙ መግለጻቸው ተሰማ፡፡
የኢትዮጵያን የልማት እንቅስቃሴ ለመገደብና ጥላሸት ለመቀባት የሚደረግ የሰብዓዊ መብት አቀንቃኞች ዘመቻ መሆኑን፣ የኢትዮጵያ ጨርቃ ጨርቅ ልማት ኢንስቲትዩት በመግለጽ አጣጥሎታል፡፡
ሁለቱ ታዋቂ የጨርቃ ጨርቅ ኩባንያዎች በበርካታ የዓለም አገሮች ሰፊ ቅርንጫፍ መደብሮች እንዳሏቸው የሚታወቅ ሲሆን፣ በኦሞ ሸለቆ ከሚመረት ጥጥ ጋር ግንኙነት እንደሌላቸው ማሳወቅ የጀመሩት ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ነው፡፡ ምክንያቱ ደግሞ የምዕራብ የሰብዓዊ መብት አቀንቃኝ ተቋማት የኦሞ ሸለቆ ነዋሪዎች ከመሬታቸው በመንግሥት እንዲፈናቀሉ ተደርገው መሬቱ ለጥጥ ምርት መዋሉ፣ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ነው በሚል ባናፈሱት መረጃ ነው፡፡ ሁለቱ ታዋቂ ኩባንያዎች ደግሞ የሰው ልጆችን ሰብዓዊ መብትና የአካባቢ ጥበቃ እንደሚያስከብሩ የሚያሳውቁ በመሆናቸው ነው፡፡
ኩባንያዎቹ ከሁለት ዓመት በፊት ቢሯቸውን በአዲስ አበባ ከፍተው በኢትዮጵያ ጨርቃ ጨርቅ ኩባንያዎች የተመረቱ ጨርቆችን በጥሩ ዋጋ መግዛት መጀመራቸው ይታወሳል፡፡ በመጀመርያ የጀርመኑ ኩባንያ ቼቦ ነው በኦሞ ሸለቆ የሚመረት የጥጥ ምርቶች መቀበል ማቆሙን የገለጸው፡፡ በዚህ ሳምንት ኤኮ ቴክስታይል በተባለው ድረ ገጽ በጉዳዩ ላይ መረጃ የሰጠው ኤችኤንድኤም መሬት መቀራመትን (ላንድ ግራቢንግ) እንደ ሰብዓዊ መብት ጥሰት ስለሚወስድ እንደሚቃወም ገልጿል፡፡ ድርጊቱ በተጨማሪም የተባበሩት መንግሥታትን የሰብዓዊ መብት መርህና የኤችኤንድኤም ድርጅትን የሰብዓዊ መብት ፖሊሲ እንደሚጥስ አክሏል፡፡ በመሆኑም በዋናነት የጨርቃ ጨርቅ ምርት ለሚያቀርብለት የቱርኩ አይካ አዲስ በዚህ አካባቢ የተመረተ ጥጥ ተጠቅሞ የሚያመርተውን ጨርቅ እንዳያቀርብለት ማሳወቁን ገልጿል፡፡
የኢትዮጵያ ጨርቃ ጨርቅ ልማት ኢንስቲትዩት ጨርቃ ጨርቅ ኩባንያዎችንና ልማቱን የሚደግፍ፣ ገበያና አዲስ ቴክኖሎጂዎችን ወደ አገር የሚያቀርብ የመንግሥት ተቋም ነው፡፡ የተቋሙ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ባንተይሁን ገሠሠ በጉዳዩ ላይ ተጠይቀው፣ የዚህ ዓይነቱ ዘመቻ የሰብዓዊ መብት አቀንቃኝ ነን ባዮች ተግባር መሆኑን ጠቅሰው፣ የጥጥ ልማት በሚከናወንበት አካባቢ መንግሥት እንኳን ሰው ሊያፈናቅል ቀርቶ እያሰባሰበ የልማት ተጠቃሚ እያደረገ ነው ብለዋል፡፡
በአካባቢው በጣም ጥቂት አርብቶ አደሮች ብቻ የሚኖሩበት ለእርሻ የሚመች በጣም ግዙፍ መሬት መኖሩን የጠቀሱት ኃላፊው፣ ‹‹አርብቶ አደሮቹ ሳር ካለ በአካባቢው ይቆያሉ፡፡ ከሌለ አካባቢውን ለቀው ይንቀሳቀሳሉ፡፡ ከዚህ ውጪ ሰው ያልሠፈረበት አካባቢ ነው፤›› ብለዋል፡፡ አርብቶ አደሮቹ በአካባቢው ረግተው እንዲቆዩና ቋሚ የእርሻ መሬት ማረስ እንዲለምዱ መንግሥት እያስተባበረ እንደሚገኝና በአሁኑ ወቅትም 80 ሔክታር መሬት ላይ አርብቶ አደሮቹን በማስለመድ ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡
ለጥጥ እርሻ የተዘጋጀ 116,859 ሔክታር መሬት በአካባቢው በአሁኑ ወቅት መኖሩንና ከዚህ ውስጥ የለማው 70,867 ሔክታር ብቻ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ በአካባቢው ጥጥ በማምረት ላይ የሚገኙ 22 ኩባንያዎች መኖራቸውንና በአሁኑ ወቅት ከተዘጋጀው 116 ሺሕ ሔክታር መሬት በላይ ማስተናገድ እንደሚችልም ጠቁመዋል፡፡ ‹‹የሰብዓዊ መብት አቀንቃኞቹን ዘመቻ መንግሥትም፣ እኛም፣ ኤችኤንድኤምና ቼቦም ያውቁታል፡፡ እኔ እስከማውቀው ድረስ አሁንም እነዚህ ኩባንያዎች ከኢትዮጵያ እየገዙ ነው፤›› ብለዋል፡፡ ጉዳዩን በተመለከተ የአይካ አዲስ የሥራ ኃላፊዎች ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ጨምሮ ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል፡፡
“የስርዓቱን አረመኔያዊ እርምጃ እናወግዛለን!”- የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ጥምረት
በተቃውሞ ሰልፉ በአንድነት ፓርቲ አመራርና አባላት እንዲሁም ሌሎች ዜጎች ላይ በፖሊስ የተፈፀመውን ድብደባ የ9ኙ ትብብር ፓርቲዎች ጥምረት አውግዟል፡፡ የ9ኙ የትብብር ፖለቲካ ድርጅት መኢአድ፣ሰማያዊ፣የኦሞ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት፣ የከንባታ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅትና ሌሎች አባላትን ያቀፈ የፖለቲካ ጥምረት ድብደባውን በፅኑ አውግዟል፡፡ ሙሉ መግለጫውን ከዚህ በታች ይገኛሉ፡-
የስርዓቱን አረመኔያዊ እርምጃ እናወግዛለን!
ከ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር የተሰጠ መግለጫ
የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር አብሮ ስለመስራትና ሌሎቹም ትብብሩን እንዲቀላቀሉ በየጊዜው የሚወተውተው አገራችን በዚህ ዘመን በማይመጥን አምባገነንና የጭካኔ ስርዓት ውስጥ የምትገኝ መሆኑን በመረዳቱ ነው፡፡ ይህ የህወሓት/ኢህአዴግ አምባገነንና ጨካኝ ስርዓት ህዳሩ 27/28 2007 ዓ.ም የአዳር ሰላማዊ ሰልፍ ላይ በወጡት አመራሮቻችን፣ አባላቶቻችን፣ ደጋፊዎቻችንና በየጎዳናው የተገኙት ንፁሃን ላይ ከፍተኛ ድብደባና የጅምላ እስር በመፈፀም ስርዓቱን ለመታገል የተነሳነበትን አላማ ትክክለኝነት አረጋግጦልናል፡፡
በዛሬው ዕለትም ገዥው ፓርቲ በፓርቲያቸው የውስጥ ጉዳይ ገብቶ የሚፈፅመውን ደባ፣ ምርጫ ቦርድንና የህዝብ ሚዲያን ተጠቅሞ ፓርቲውን ለመከፋፈልና አሳንሶ ለማሳየት የሚያደርገውን እኩይ ተግባር በመቃወም ሰልፍ የወጡ የአንድነት አመራሮች፣ አባላት፣ ደጋፊዎችና የፓርቲው ጽ/ቤት ፊት ለፊት የሚገኘው ቤተ ክርስትያን አካባቢ የነበሩ አዛውንት ምዕመናንን ሳይቀር በመደብደብ ጭካኔውን ዳግመኛ አሳይቶናል፡፡ ፖሊስ በትዕዛዝ በአንድነት አባላት ላይ ከፍተኛ የጭካኔ እርምጃ ወስዷል፡፡ አብዛኛዎቹንም በጅምላ አስሯል፡፡
ስርዓቱ በእነዚህ ሰላማዊ ዜጎች ላይ አሁንም የጭካኔ እርምጃውን መድገሙ ስልጣኑን የማጣት ከፍተኛ ስጋት ውስጥ እንዳለ እና ከይስሙላ ያለፈ ለሰላማዊ ትግሉ ዝግጁ አለመሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡ ትብብራችን የስርዓቱን ጨካኝነት እያወቁም ቢሆን በሰላማዊ መንገድ ጥያቄያቸውን ለማቅረብ በስርዓቱ የማይከበረውን ህገ መንግስታዊ መርህ ተከትለው ሰልፍ ለወጡ ቆራጥ የአንድነት አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች አድናቆቱን መግለጽ ይወዳል፡፡ መስዋዕትነታችሁ ለነገ ድላችን ስንቅ በመሆኑ ይበልጡን ተጠናክራችሁ በጋራ ትግላችን እንደምናጠናክርም እምነታችን ነው፡፡
በተቃራኒው ገዥው ፓርቲ ህግ የማክበርና የማስከበር ሚናውን ረስቶ ፖሊስ፣ ደህንነትንና ሌሎች ተቋማትን ለራሱ ስልጣን ማስጠበቂያ በማዋል በአንድነት አመራሮች፣ አባላት፣ ደጋፊዎች ላይ የፈፀመውን ለዘመኑ የማይመጥንና በሰላማዊ መንገድ መብታቸውን ለጠየቁት ኢትዮጵያውያንም የማይገባ የጭካኔ እርምጃ በጥብቅ እናወግዛለን፡፡
ኢትዮጵያውያንን የማስተዳደር አቅምና ሞራል ያጣው ገዥው ፓርቲ የዜጎችን ጥያቄ በኃይል ማዳፈን የማይቻል መሆኑንና አገራችን ወደባሰ ችግር እንደሚከታት ተረድቶ ከዚህ የጭካኔ እርምጃው እንዲቆጠብ፣ እርምጃውን የወሰዱትን አካላት በህግ ተጠያቂ እንዲሆኑና የታሰሩትን በአስቸኳይ እንዲፈታ እናሳስባለን፡፡ ፖሊስ፣ ደህንነት፣ መከላከያና ሌሎች ተቋማት ገዥው ፓርቲ አላፊ መሆኑን በመገንዘብና ከገዥው ፓርቲ ታዛዥነት በመውጣት ወገኖቻቸሁ ላይ እንዲህ አይነት የጭካኔና አሳፋሪ እርምጃ ከመውሰድ ተቆጥባችሁ ከህዝብ ጎን እንድትቆሙ ጥሪያችን እናቀርባለን፡፡
ያለ መስዋዕትነት ድል የለም!
ጥር 17/2007 ዓ.ም
አዲስ አበባ















